Get Mystery Box with random crypto!

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

የቴሌግራም ቻናል አርማ yetewahedoarbegnoch — የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch
የቴሌግራም ቻናል አርማ yetewahedoarbegnoch — የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch
የሰርጥ አድራሻ: @yetewahedoarbegnoch
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.53K
የሰርጥ መግለጫ

#ኢትዮጵያ_የዓለም_ብርሃን
ክንድህን ኃይልህንም ጽድቅህንም እስክነግር ድረስ አቤቱ አትተወኝ
#መዝሙር_ዳዊት 70 ( 71 ) 15 – 18

"የመለከቱን ድምፅ የሚሰማ ሰዉ ባይጠነቀቅ፥ ሰይፍ መጥቶ ቢወስደዉ፥ ደሙ በራሱ ላይ ይሆናል።
"የመለከቱን ድምፅ ሰምቶ ስላልተጠነቀቀ ደሙ በራሱ ላይ ይሆናል፤ ቢጠነቀቅስ ኖሮ ነፍሱን ባዳነ ነበር።"
#ትንቢተ_ህዝቅኤል 33፡4-5

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-08-30 18:21:14
ለምትቃወሙን እና ለምታሳድዱን
#ልዑል_እግዚአብሔር_በዮሐንስ_ወንጌል_ምንድነው_ያለው:-
'' እኔ በአባቴ ዘንድ ያየሁትን እናገራለሁ፤ እናንተም ደግሞ በአባታችሁ ዘንድ ያያችሁትን ታደርጋላችሁ።''
የዮሐንስ ወንጌል 8 : 38

ስለዚህ በዚህ ዘመንን በሚመዝን ሕያው ቃል መሠረት እኛ የኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን ቤተሰቦች ከአምላካችን ከአባታችን እግዚአብሔር ያየነውን እና የሰማነውን፣ ሐዋርያት፣ ነቢያት፣ ጻድቃን አባቶቻቸን ያስጨበጡንን እውነት እንመሰክራለን ፤ እናንተ(አሳዳጆቻችን) ደግሞ ከአባታችሁ ከዲያብሎስ ያያችሁትን ታደርጋላችሁ።

''እናንተ ከአባታችሁ ከዲያብሎስ ናችሁ የአባታችሁንም ምኞት ልታደርጉ ትወዳላችሁ። እርሱ ከመጀመሪያ ነፍሰ ገዳይ ነበረ፤ እውነትም በእርሱ ስለ ሌለ በእውነት አልቆመም። ሐሰትን ሲናገር ከራሱ ይናገራል፥ ሐሰተኛ የሐሰትም አባት ነውና።'' የዮሐንስ ወንጌል 8 : 44

'' እኔ ግን እውነትን የምናገር ስለ ሆንሁ አታምኑኝም።''
የዮሐንስ ወንጌል 8 : 45

''ከእግዚአብሔር የሆነ የእግዚአብሔርን ቃል ይሰማል፤ እናንተ ከእግዚአብሔር አይደላችሁምና ስለዚህ አትሰሙም።''
የዮሐንስ ወንጌል 8 : 47

እግዚአብሔር ይመስገን! እመብርሃን ትክበር ትመስገን!!!
622 viewsedited  15:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 16:33:26
በእስ*ላሞች ዘንድ በተለይም በዚሁ በመካ መዲና ዙሪያ እስላሞች ባሉበት ሁሉ የሚታመንና የሚነገር አንድ አባባል ወይም ትንቢት አለ ፡፡
እሱም እንዲህ ነው ፦
ወደፊት በኢትዮጵያ ምድር የሚነሳ አንድ መላጣ የሆነ ንጉስ ይመጣል / ይነግሳል / ይህ ሰው እስል*ምናንና እንዲሁም ዋናውን ሥፍራ መካ መዲናን ያፈር*ሳል ጥቂት ሰው ብቻ ነው የሚተርፈው የተቀረው ይጠ*ፋል ብለው ያምናሉ ፡፡

ይህን አባባል የቀደሙ በእድሜያቸው የገፉ አባት እስላ*ሞች ባብዛኛው የሚያውቁት ነው ፡፡ ወጣቱ እስ*ላም ብዙም ቦታ አይሰጠውም ነገሩ ግን እውነት ነው ፡፡ መቼም በየዘመኑ እግዚአብሔር የሚወደው አንዳንድ የዋህ ሰው ከየትኛውም ሥፍራ አይጠፋምና አንዱ የዋህ እስ*ላም ተገልጦለት ይሆናል ፡፡ የሆነ ሆኖ እስል*ምና እጅግ ብዙ የንፁሃንን ደ*ም ያፈ*ሰሰ በመሆኑ በእርግጥም ይጠ*ፋሉ ይጠ*ረጋሉ ፡፡
ከኢትዮጵያ የአለም ብርሃን መልእክት 9 የተወሠደ፡፡
732 views13:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 12:43:58
በመጀመሪያ ነፃ የምትወጣው ነፃ አውጭዋ ሀገር ኢትዮጵያ ናት!
#የእግዚአብሔር_ቃል_እንዲህ_ይላል፦
'' አንዱን ከሰሜን አነሣሁ መጥቶአልም፤ አንዱም ከፀሐይ መውጫ ስሜን የሚጠራ ይመጣል፤ በጭቃ ላይ እንደሚመጣ ሰው አፈርም እንደሚረግጥ ሸክለኛ በአለቆች ላይ ይመጣል። '' ትንቢተ ኢሳይያስ 41 : 25

'' በመጀመሪያ ለጽዮን። እነኋቸው እላለሁ፤ ለኢየሩሳሌምም የምስራች ነጋሪን እሰጣለሁ። '' ትንቢተ ኢሳይያስ 41 : 27

እግዚአብሔር ይመስገን! እመብርሃን ትክበር ትመስገን አሜን!!
895 viewsedited  09:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 09:44:31 አረሳት ኢትዮጵያን በእርፈ መስቀል
አባ ተክለሃይማኖት ሰባኬ ወንጌል።
627 viewsedited  06:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 09:11:11
ወርኅ ነሐሴ ፳፬

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ነሐሴ ሃያ አራት ጌታችን በቅዱስ አምላካዊ ቃሉ ‹‹ሐዲስ ሐዋርያ›› ብሎ የሰየማቸው የኢትዮጵያ ብርሃኗ የሆኑ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ዕረፍታቸው ነው፡፡ ምግባር ሃይማኖት፣ ገድል ትሩፋታቸው ከማር የጣፈጠ ሰማዕቱ አቡነ ቶማስ ዘመርዓስ ዕረፍታቸው ነው፡፡ ለ12 ዓመታት በጉድጓድ ውስጥ በተጋድሎ የኖረች እንዲሁም በጣና ባሕር ውስጥ ገብታ ሰውነቷ ተበሳስቶ የባሕር ዓሣ መመላለሻ እስከሚሆን ድረስ እንደ ተተከለ ዓምድ ሆና ከባሕሩ ሳትወጣ 12 ዓመት ቆማ ስትጸልይ የኖረችው እናታችን ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ዕረፍቷ ነው፡፡

❖ የቅዱስ አባታችን አቡነ ተክለሃይማኖት አብይት በዓላት እነዚህ ናቸው፦
መጋቢት 24 ቀን 1196 ዓ.ም ፅንሰታቸው
ታኅሣሥ 24 ቀን 1197 ዓ.ም ልደታቸው
ኅዳር 24 ቀን ከ24ቱ ካህናተ ሰማይ ጋር በሕይወተ ሥጋ እያሉ የሥላሴን መንበር ያጠኑበት ሲሆን
ጥር 4 ቀን 1289 ዓ.ም ደግሞ በጸሎት ብዛት አንድ እግራቸው የተሰበረበት ነው (ነገር ግን የዕረፍታቸውን ቀን ይዞ በዚሁ በጥር ወር በ24 ይከበራል)
ነሐሴ 24 ቀን 1296 ዓ.ም ዕረፍታቸው
በግንቦት 12 ቀን 1353 ዓ.ም ፍልሰተ ዐፅማቸው ነው፡፡

«ስማቸውን ከሚጠሩት ነፍሳት ሁሉ ጻድቅም ቢሆን ኃጥእም ቢሆን ወደ ክቡር አባታችን ተክለ ሃይማኖት ሳያደርሱት ወደ ዘላለም ርስቱ ወይም ወደ ሲኦል አያገቡትም»

[አርኬ]
ሰላም ዕብል እንበለ አርምሞ በጽዋዔ፡፡ ኪያከ አበ ወኪያከ ረዳዔ፡፡ ተክለ ሃይማኖት መዋዒ እንዘ ትጸንሕ ተስፋ ትንሣኤ፡፡ አጽናዕከ ለቀዊም አእጋረ ክልኤ፡፡ ወእምስቴ ማይ አህረምከ ጕርዔ፡፡

የከበረች ቃልኪዳናቸው ኹላችንንም ከመከራ ሥጋ ከመከራ ነፍስ ይጠብቀን! አሜን!
t.me/AlphaOmega930
654 views06:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 09:08:40
እንኳን ለኢትዮጵያዊቷ እናታችን ለቅድስት ክርስቶስ ሰምራ አመታዊ መታሰቢያ በአል በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ።

#ነሐሴ_24
በዚች እለት የጌታ ወዳጅ የነፍሳት አማላጅ፣የእናታችን የቅድስት ክርስቶስ ሰምራ የዕረፍቷ መታሰቢያ እለት ነው።

የእናታችን ብፅዕት ቅድስት ክርስቶስ ሰምራ ልመናዋ አማላጅነቷ ከእኛ ጋር ይኑር ለዘላለሙ አሜን፫
650 views06:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 09:03:16
እንኳን አደረሳችሁ አደረሰን!!!
#ነሐሴ_24
በዚህችቀን ታላቅ የከበረ ሐዲስ ሐዋርያ #አባታችን_ተክለሃይማኖት አረፈ፣ የከበረች #ቅድስት_ክርስቶስ_ሠምራ የዕረፍቷ መታሰቢያ ነው፣ የክርስቶስ የመርዓስ ኤጲስቆጶስ #ቅዱስ_አባት_ቶማስ_አረፈ።
686 views06:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 19:05:24 #የአለም_ሰዉ፦ አባ! መንግስታችን እኮ ብዙ ቱሪስት የሚስቡ ፓርኮችን እየሰራ ኢትዮጵያን ሊያበለፅጋት ነዉ!!!
#የእምነት_ሰዉ፦ አየ ልጄ ! ግን መጀመሪያ የሚመጡት ቱሪስቶች ከመጣዉ ከባድ የእግዚአብሄር ቁጣ እና ቅጣት(ጠረጋ) ይትረፋ እስቲ።
ቱሪስቶቹ የሚመጡበት ሀገር እኮ በቁጥር 1 አምላክን የካዱ፣ እጅግ ያስከፋ...ናቸዉ። "አንቸኩል እንጅ የእግዚአብሄርን ቅን ፍርድ በቅርቡ እናየዋለን።"
721 views16:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 19:02:37 ኢትዮጵያ የተወደደች የተመረጠች በዘመን ጉዞዋ አምላኳን ያከበረች ፣ ያንንም አምልኮ ከልቡ የሚፈፅም ሕዝብ በውስጧ እስከዛሬ ይዛ የዘለቀች ናት፡፡ ይህ እውነት ይህ ብርሃን ዲያብሎስን ያለ እረፍት የሞቶ መርዶውን ተሸክሞ እንዲዞር አድርጎታል፡፡

ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት 9
762 views16:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 18:59:08
ነሐሴ 24
እንኳን ለኢትዮጵያዊዉ ቅዱስ አባታችን አቡነ ተክለሐይማኖትና ለኢትዮጵያዊቷ ቅድስት እናታችን ክርስቶስ ሠምራ ዓመታዊ የእረፍት መታሰቢያ በዓል አደረሰን! አደረሳችሁ! የቅዱሳኑ ምልጃና በረከት አይለየን! አሜን!
1.1K views15:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ