2022-08-30 09:11:11
ወርኅ ነሐሴ ፳፬
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ነሐሴ ሃያ አራት ጌታችን በቅዱስ አምላካዊ ቃሉ ‹‹ሐዲስ ሐዋርያ›› ብሎ የሰየማቸው የኢትዮጵያ ብርሃኗ የሆኑ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ዕረፍታቸው ነው፡፡ ምግባር ሃይማኖት፣ ገድል ትሩፋታቸው ከማር የጣፈጠ ሰማዕቱ አቡነ ቶማስ ዘመርዓስ ዕረፍታቸው ነው፡፡ ለ12 ዓመታት በጉድጓድ ውስጥ በተጋድሎ የኖረች እንዲሁም በጣና ባሕር ውስጥ ገብታ ሰውነቷ ተበሳስቶ የባሕር ዓሣ መመላለሻ እስከሚሆን ድረስ እንደ ተተከለ ዓምድ ሆና ከባሕሩ ሳትወጣ 12 ዓመት ቆማ ስትጸልይ የኖረችው እናታችን ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ዕረፍቷ ነው፡፡
❖ የቅዱስ አባታችን አቡነ ተክለሃይማኖት አብይት በዓላት እነዚህ ናቸው፦
መጋቢት 24 ቀን 1196 ዓ.ም ፅንሰታቸው
ታኅሣሥ 24 ቀን 1197 ዓ.ም ልደታቸው
ኅዳር 24 ቀን ከ24ቱ ካህናተ ሰማይ ጋር በሕይወተ ሥጋ እያሉ የሥላሴን መንበር ያጠኑበት ሲሆን
ጥር 4 ቀን 1289 ዓ.ም ደግሞ በጸሎት ብዛት አንድ እግራቸው የተሰበረበት ነው (ነገር ግን የዕረፍታቸውን ቀን ይዞ በዚሁ በጥር ወር በ24 ይከበራል)
ነሐሴ 24 ቀን 1296 ዓ.ም ዕረፍታቸው
በግንቦት 12 ቀን 1353 ዓ.ም ፍልሰተ ዐፅማቸው ነው፡፡
«ስማቸውን ከሚጠሩት ነፍሳት ሁሉ ጻድቅም ቢሆን ኃጥእም ቢሆን ወደ ክቡር አባታችን ተክለ ሃይማኖት ሳያደርሱት ወደ ዘላለም ርስቱ ወይም ወደ ሲኦል አያገቡትም»
[አርኬ]
ሰላም ዕብል እንበለ አርምሞ በጽዋዔ፡፡ ኪያከ አበ ወኪያከ ረዳዔ፡፡ ተክለ ሃይማኖት መዋዒ እንዘ ትጸንሕ ተስፋ ትንሣኤ፡፡ አጽናዕከ ለቀዊም አእጋረ ክልኤ፡፡ ወእምስቴ ማይ አህረምከ ጕርዔ፡፡
የከበረች ቃልኪዳናቸው ኹላችንንም ከመከራ ሥጋ ከመከራ ነፍስ ይጠብቀን! አሜን!
t.me/AlphaOmega930
654 views06:11