ከአሏህ መልካም ነገር እንጂ አታስብ ለአንድ የአረብ ዘላን: አንተኮ ሟች ነህ አሉት… አርሱም አለ: ከዚያስ ወዴት እሄዳለሁ? ወደ አሏህ አሉት እርሱም: ኸይርን ከአሏህ እንጂ አግኝተን አናውቅ… ታዲያ ከርሱ ጋር መገናኘትን እንፈራለን እንዴ! ከአሏህ መልካምን ማሰብ ምነኛ ያማረ ነው!! ከሰለፎች አንዱ ተጠየቀ: ዱዓው ተቀባይነት ያለውን ሰው ታውቃለህን? እርሱም አላቸው: አላውቅም። ግን ዱዓን የሚቀበለውን አውቃለሁ! ከአሏህ መልካምን ማሰብ ምነኛ ያማረ ነው!! አንዱ ኢብኑ ዐባስን ጠየቃቸው: ለቂያም ለት ማን ነው ሰውን የሚመረምረው? ኢብን ዐባስ: አሏህ ብለው መለሱለት። ሰውየውም አለ: በከዕባ ጌታ እምላለሁ ዳንን!! ከአሏህ መልካምን ማሰብ ምነኛ ያማረ ነው!! አንድ ወጣት ሞትን ሲያጣጥር እናቱ አለቀሰች… ወጣቱ: አማዬ የኔን ስራ አንቺ የምትመረምሪው ቢሆን እንዴት ታደርጊ ነበር? እናት: አዝንልክ ነበር። ወጣቱም አላት: አሏህ ካንቺ የበለጠ ለኔ አዛኝ ነው!! ከአሏህ መልካምን ማሰብ ምነኛ ያማረ ነው! 111 views˙·٠•● Abuki ●•٠·˙, 19:30