Get Mystery Box with random crypto!

ይሰበካል የእዉነት ወንገል

የቴሌግራም ቻናል አርማ yeihunetwongel — ይሰበካል የእዉነት ወንገል
የቴሌግራም ቻናል አርማ yeihunetwongel — ይሰበካል የእዉነት ወንገል
የሰርጥ አድራሻ: @yeihunetwongel
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 720
የሰርጥ መግለጫ

ወደ አለም ሀሉ ሂዱ ወንገልን ለፍጥረት ሁሉ ስበኩ፡፡ያመነ የተጠመቀ ይድናል ያላመነ ግን ይፈረድበታል፡፡ማርቆስ 16:15
@Any comment
@Altishyeapo

Ratings & Reviews

4.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-06-17 08:33:13 #NEW_SINGLE_APOSTOLIC_SONG

Singer Bro Yosef Sultan

አውቀው ነው የማመልከው 2*
ፈቅጄ ነው ማመስግነው

FROM MISRAK SHEWA #DUKEM_ATBIA

Size 4.38 MB
Time 4:34

@MARANATHAWOCH
@MARANATHAWOCH

የመወያያ ግሩፕ @marantawoch

ሌለም አድስ መዝሙር በቅርብ ቀን ይለቀቃል ይጠብቁን!!!
307 views05:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-07 14:20:44 ኖረህ አሳይ!!!

አልቃሻ ደካማ ትውልድ
ላየው ሁሉ የሚያጎበድድ
በሀጢያት ሞቶ እሁድ የሚወለድ

ሳያረጅ ያረጀ ልፍስፍስ
ውስጡ ኦና እላዩ ቅልስልስ
ላገኘው ሁሉ እጅ የሚያነሳ አቅመ ቢስ
እንደ ፈሳሽ ውኃ ሰው ባበጀው ቦይ ውስጥ ዝም ብሎ የሚፈስ

ከኮንፍረንስ መልስ የኢየሱስ ወቶአደር
ፃዲቅ ልበ ሙሉ የሚሸልል የሚፎክር
አቀንቃኝ ይሆናል ደርሶ ስለ እግዚአብሔር
የሁሉም ሰው ተመሳሳይ ነው ፕሮፋይል ፒክቸር

ከሳምንት ቦሀላ አቋም ይቀየራል
ቀንደኛ ተሟጋች ወላይታ ነኝ ይላል
ይፅፋል ይለጥፋል
ይታገላል ያታግላል
አዳምን ማውለቁን ጭራሽ ይዘነጋል

ደግሞ ሌላኛው
መብታችን ይከበር ድምፃችን ይሰማ
ክልል ይሰጥ ይላል ለእኛ ለሲዳማ
ተሸክሟል መፈክር
በአንዱ እጁ ለሲዳማ በሌላኛው ለእግዚአብሔር

ደግሞ ሌላኛው
ኦሮሞ ነኝ እኔማ
ዝም አልልም መሬታችን ሲቀማ
ህዝባችን ሲጎዳ ሲፈናቀል
እንታገል ዝም አንበል እያለ ይደራጃል
ዘር ለመቀየር መጠመቁን ይዘነጋል

ደግሞ ሌላኛው
ሌላው አይኑር ከእኔ በቀር
የአባይ ልጅ የበላይ ዘር
ዋልታ ነኝ ይላል ለዚህች አገር
ቆይቶ ትሰማለህ ሲዘምር
እያለ ሰማይ ነው የኔ ሀገር

ብኩን ትውልድ ዳተኛ
ሰነፍ ትውልድ ዘረኛ

ብቻ ኮንፍረንስ ይድረስ
ንስሀ የሚገባ የለም እንደሱ የሚያለቅስ

መለጠፍ አይበቃም ፕሮፋይልህ ላይ
የተማርከውን ነገር አኑር በልብህ ላይ
በሕይወትህ ተግብረው ለሁሉ እንዲታይ
ኖረህ አሳይ

@MARANATHAWOCH
@MARANATHAWOCH

የመወያያ ግሩፕ @marantawoch
305 views11:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-01 00:16:00 #የልብስና_የአለባበስ_ነገር ( ለብዙዎች በረከት የሆነች ት/ት /

#ልብስ ለሌላው ሰው መታየት የሌለባቸው የሰውነት ክፍሎቻችንን ለመሸፈን እንዲሁም በልብሱ ዲዛይን ምክንያት የሚገኘውን ውበት ለመላበስ የሚለበስ ነው። ሌሎችም ብዙ ጥቅሞች ሊኖሩት እንደሚችሉ እሙን ነው። ሰዎች እንደየ አቅማቸው ያምርብኛል የሚሉትን ልብስ ገዝተው ወይም አሰርተው ይለብሳሉ! ሴቶችም ወንዶችም።

#አለባበስ ጋ ስንመጣ ብዙ ጊዜ አለባበሳቸው የሚመለከታቸውን ሰው ወደሌላ ነገር(ምኞት) ይመራል በሚል እህቶች ላይ ቅሬታ ሲቀርብ ይስተዋላል! አንዳንድ እህቶችም "እህቴ እንዲህ ባትለብሺ ጥሩ ነው"የሚል ምክር ሲሰጣቸው ከመቀበል ይልቅ " ስለእከሌ ምን አገባኝ ደግሞስ ማን እየኝ አለው!" የሚል ከመፅሃፍ ቅዱስ እይታ ውጭ የሆነ መልስ ሲመልሱ ይስተዋላል።

#እህቴ የፈለግሽውን ልብ መልበስሽ መብትሽ ነው ነገር ግን ያ የለበስሽው ልብስ የሚያይሽን ሰው በውስጡ ስጋዊ ምኞት የሚፈጥርበት ከሆነ አንቺም ይህም ወንድም በጥፋት ውስጥ ትሆናላችሁ። ስለዚህ ነው የምትለብሺው ልብስ ውበትሽን ከመጠበቅና ሰውነትሽን ከመሸፈን አልፎ በተመልካች ልብ ውስጥ ኃጢአት እንዲወለድ የሚያደርግ ምኞት እንዲፀነስ እንዳያደርግ ነው አለባበስሽን ማስተካከል ያለብሽ

አንዳንድ እህቶች ጡታቸውን፣እምብርታቸውን፣ታፋቸውን፣ዳሌያቸውን የሚያሳይ ልብስ ይለብሳሉ። ብዙ ወንዶችንም ይስባሉ! እህቴ እርግጠኛ መሆን ያለብሽ ነገር ጡትሽን አይቶ የመጣ ወንድ አንቺን ፈልጎ ሳይሆን ጡትሽን ነው። #አንቺ_ደግሞ_ጡትሽ_አይደለሽም
አንዳንድ የሰውነታችን ክፍሎች በልብስ እንዲሸፈኑ የተደረጉት በቀላሉ እንዳይገኙና የፈለጋቸው አካል ዋጋ መክፈል እንዳለበት ለማሳወቅም ጭምር ነው። ገላለጥሽው ማለት ግን ዋጋውንና ዋጋሽን አሳጣሽው ማለት ነው።

#ወንድሞች

የአለባበስ ጉዳይ ብዙ ጊዜ እህቶች የሚወቀሱበት ነገር ቢሆንም አንዳንድ ወንድሞችም ስሜት ቀስቃሽና ፍኞት ፈጣሪ ልብስ ሲለብሱ ይስተዋላሉ!
ለምሳሌ:-
ከእህቶች ጋር ሲሆን የደረት ቁልፍ በመክፈት ደረትን ማሳየት(ጡትን ከፍቶ እንደማሳየት ይቆጠራል)
የብልትን ቅርፅ የሚያሳይ ሱሪ መልበስ ሴት ልጅ በጣም ስስ ታይት እንዳደረገች ያክል ነው።

በነገራችን ላይ እህቶችም ወንድሞችም አንድን ልብስ ስትለብሱ ያምርብኛል፣ሌሎች ወደኔ እንዲሳቡ ያደርጋል በሚል እይታ ስለሆነ ማማሩ የሚደገፍ ቢሆንም ልብሳችሁን አይቶ የመጣው ሰው በስሱ ወይም በግላጭ የሆነ ውድ ነገር ስላሳያችሁት እንጂ እናንተነታችሁን ፈልጎ ላይሆን ይችላል! ስለዚህ ውድ የሆነ ማንነታችሁን በተገላለጠ ልብስ አታሳንሱት!

ምርጥ አለባበስ ማለት ለራስ ውበት እያሰቡ ለሌላውም እያሰቡ ሲሆን ነው።
ክርስትና ለጌታም ለሰዎችም መኖር ነው! ክርስትና እንደፈለኩኝ ብሆን ሌላ ሰው ምን አገባው የሚባልበት አይደለም!

ክርስቲያን ነሽ/ህ አዎ ከሆነ መልሱ በአለባበስሽ/ህ ጌታን አ
ክብር/ር ለሰዎች ፈተና አትሁኚ/ን።

@MARANATHAWOCH
@MARANATHAWOCH

የመወያያ @Marantawoch
453 views21:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-03 12:02:18
የሰፈረ ሰላም አጥብያ የኮሌጅ እና ዩኒቨርስቲ የተማሪዎች ሕብረት

#የስነ_ጽሁፍና_የመዝሙር_ፈስትቫል

ግምቦት 6-7 / 2014 ዓ/ም

በዕለቱ፦ ☞ የተለያዩ ስነ-ጽሁፍ
☞ ሶሎ መዝሙር
☞ ኳየር መዝሙራቸውን ያቀርባሉ
☞ የእግዚአብሔር ቃል ይሰበካል
☞ እግዚአብሔር በክብር ይመለካል

አዳድስ የኮሌጅ እና ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች #WELLCOME ፕሮግራም ይደረጋል

ኑ ሁላችሁም ተጋብዛችኋል!!

@MARANATHAWOCH
@MARANATHAWOCH
465 views09:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-29 19:41:04 የአንድ አምላክ ልጆች! በተለይ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ይህንን pdf ያነበበ እጁን ያውጣ። ነገር ግን አላነበብኩም የሚል ካሌ ማንበብ ግዴታ ባይሆንም በትህትና እለምናችኋለሁ። ዘንድሮም ዩኒቨርስቲ የሚትገቡ ተማሪዎች እባካችሁ ለትምህርታችሁም ሆነ ለኑሮአችሁ ከኢየሱስ ጋር ተጣብቃችሁ የሚትኖሩበት ህይወት ሊመራችሁ ስለሚችል አምብባችሁ ተባረኩበት።

የአንድ አምላክ ልጆች ይለይ pdf

የተለግራማችን ቻናል፦

@MARANATHAWOCH
@MARANATHAWOCH

የመወያያ ግሩፕ @marantawoch

any comment @Taddyapostolic
435 views16:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-27 22:03:04 @Yeihunetwongl
#አላውቅም ምክንያቱ።

አንተ ስትለየኝ ምድር ታስከፋኛለች
እህል በትኜባት እሾህ ታበቅላለች

አንተ ስትለየኝ ሰው አይረዳኝም
በፊቱ እያነባሁ ዞር ብሎ አያየኝም

አንተ ስትለየኝ ተስፋ ከእኔ ይርቃል
ለስው እየበራ ለእኔ ይጨልማል

አንተ ስትለየኝ አጥብቄ ያሰርኩት በድንገት ይፈታል
ጨብጬ የያዝኩት ከእጄ ፈሶ ያልቃል

አንተ ስትለየኝ ፀሀይ ለእኔ አትወጣም
ለሊቱ ይረዝማል ለእኔ ቶሎ አይነጋም

አንተ ስትለየኝ አቅሜ ይከዳኛል
ቀላል ንፋስ ነፍሶ ገፍቶ ይጥለኛል

አንተ ስትለየኝ ዝም ብሎ ይከፋኛል
ሰው ሁሉ እየሳቀ እኔ እንባ ያንቀኛል

አንተ ስትለየኝ ከሰው ጋር አልገጥምም
ደስታ ከእኔ ይርቃል ሰላም አላገኝም

አንተ የልቤ ጌታ ከአፈር የፈጠርከኝ
አንተ ስትለየኝ እንዲህ ነው የሚያደርገኝ
ለአፍታ ስትለየኝ ፊትህ ከእኔ ሲዞር
የለም ወዳጄ ሆይ እኔ ያልሆንኩት ነገር

ፈጥነህ ካልደረስክልኝ ካላገኘኝ እጅህ
ባክኜ እጠፋለሁ እኔ ምስኪን ልጅህ

አንተ የነፍሴ አምላክ እባክህ እራራልኝ
ልብህ ለእኔ ይዘን ምህረትህን ላክልኝ
አንተ ስትለየኝ ሁሉን ነገር አወኩ
እኔ ያለ አንተ ምንም እንዳልሆንኩ

@yeihunetwongel
676 views19:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-25 22:57:42 Apostolic fellowship አሰተባባሪዎች ስልክ ቁጥር ከዚህ በታች

1. Wachemo University

Br Mehari Degemu
+251947708255

Sis Lemlem Petros
+251964083056

2. Asela(Arsi) University

Br Abayineh
+251909751199

Br Eyosias
09 45 03 85 29

Br Dekeba
0922427655

Sis Lidiya
+251941045516

3. Debre Berhan University
Apostolic Fellowship

Br Yoseph Gezahegn
+251 94 056 0075

Br Kaleb Mekonin
+251 92 269 2325

Sis Aster Gebisa
+251 94 741 9683

Sis Befikir Tilahun
+251 98 309 0974

4.Wolaita sodo wsu
Bro Amanule Asefa
0913466403

5.Bahiredar university

Bro simegne Aserigedew
+251927421503

Bro yonatan
+251922354563

Bro Natneal
+251965524503

ወ/ም አግዛቸው +251933814321
ወ/ም ዳግም +251923322770
6.A.A Science and Technology university

Bro Esayas siltan
+251943837887
Bro Kirubel Methewos
+251986226283

7.Oda Bulutum University

Bro Bilitasore
+251932105126

Bro.Buruki
+251975202648

Bro.Tekile
+251989045339

እስካሁን ለእኛ የደረሱን ናቸው ስለትብብራችሁ

@MARANATHAWOCH

የመወያያ ጉሩፓችን @Marantawoch
386 views19:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-19 03:36:03 ውድወንድሞችና እህቶች ቃል በገባነው መሠረት 15 pdf ልከንላችኋል። አሁንም በመቀጠል ወደ 10 የሚደርሱ pdfochin በሚቀጥለው ማታ እንልካለን። ስለዚህ በትዕግስት እንድትጠብቁን እያሳሰብን ለሌሎችንም ሼር ማድረግ አትርሱ እንላለን።

ነገር ግን ይህንን የሚንልከው በማራናታ....MARANATHA ተለግራም ቻናል ላይ መሆኑን አትዘንጉ። ምክንያቱም በሌላ ግሩፕ ላይ ሆናችሁ አልተለቀቀም እንደ እያላችሁ COMMENT እየሰጣችሁኝ ስለሆነ ይህንን ለማሳሰብ እወዳለሁ።

ለማግኘት፦ @MARANATHAWOCH
@MARANATHAWOCH JOIN አድርጉ PLS

Comment ካላችሁ @marantawoch ላይ ፃፉልን

መልካም ምንባብ!!

@Taddyapostolic
467 views00:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-17 00:08:11 ሰላም ለእናንተ ይሁን ውድ የማራናታ ተለግራም ቤተሰብ እና የኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤተ ክርስትያን ወንድሞችና እህቶች በሙሉ፦

ዛሬ ማታ " የትኛውን pdf ፈልገው አጥቷሉ" የሚል ፕሮግራም አዘጋጅተናል።

ከዚህ በታች ያሉ pdfoch በእጃችን ስለሚገኝ የፈለጉትን pdf ስሙን በ @Taddyapostolic በመላክ መሳተፍ ይችላሉ።

በጣም አስፈላጊ የሆኑትን ላኩልን። ነገር ግን pdfun የሚንለከው
በ @MARANATHAWOCH ተለግራም በኩል ስለሆነ JOIN አድርጋችሁ ጠብቁን።

ለሌሎችም #SHARE ማድረግን አትርሱ ፤ የፈለጋችሁትንም PDF ጽፋችሁ
በ @Taddyapostolic ላይ ላኩልን።

የpdf ስሞች ከዚህ በታች የተዘረዘሩት ናቸው።

1, ቃሉ ይናገር፦ በቢሾፕ ተክለማርያም የተጻፈ
2, Eschatology_ finale destiny፦ በቢሾፕ ጌታሁን ላምቤቦ
3, የአንድ አምላክ ልጆች ይለይ፦ በወ/ም ታደሰ ከWCU
4, የመዳን እውቀትን ተቀበል፦ በወ/ም ታደሰ ከWCU
5, ወደ መዳን የሚያደርስ እውነት፦ scanned by camera
6, ህይወት የሚገኝበት መንገድ፦ scanned by camera
7, የስላሴ አመጣጥ፦ በወ/ም ናቲ ከአረካ
8, ጥምቀት በእርግጥ ያድናል
9, የልደት በዓልን ስለ ማክበር መጽሐፍ ቅዱስ ምን ይላል?
10, እግዚአብሔር አንድ ነው።
11, የሥላሴ አማኞች ሊመለሱ የሚገባቸው ጥያቄዎች
12, የ666 ምልክቶች
13, የኢትዮጵያ ሐዋርያት ቤተክርስትያን አባላት መመሪያ
14, የማለዳ ትምህርት ከ1-60
15, እውነት እና ምህረት
16, አስተማሪ ትረካዎች
17, መንፈሳዊ ግጥም
18, መንፈሳዊ ወጣት
19, ዘጠኙ የመንፈስ ቅዱስ ፍሬዎች
20, ኢየሱስን ማን ይሉታል
21, የማለዳ ትምህርት ከ61-120
22, ONLY JESUS ( APK)
.
.
.
ከእነዚህ ከ1-22 ካሉት ውስጥ የፈለጉትን እስከ ቀጣዩ ሳምንት ላኩልን

#join & #share

@MARANATHAWOCH
@MARANATHAWOCH

የመወያያ ግሩፓችን @marantawoch ላይ እናወራ

ጽሁፉን በ @Taddyapostolic ይላኩ
412 views21:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-12 18:45:20 አናማርር! እንታገስ!!

ቆሮንቶስ 10:13
ለሰው ሁሉ ከሚሆነው በቀር ምንም ፈተና አልደረሰባችሁም፤ነገር ግን ከሚቻላችሁ መጠን ይልቅ ትፈተኑ ዘንድ የማይፈቅድ እግዚአብሔር የታመነ ነው።
ትታገሱም ዘንድ እንድትችሉ ከፈተናው ጋር መውጫን ደግሞ ያደርግላችኋል።

አብዛኛውን ጊዜ በተለያየ የሕይወት ፈተና ውስጥ እንወድቃለን ብዙ እንገላታለን አልፈንም እስከማማረር ድረስ እንደርሳለን።

አምላክ ለምንድነው እኔን ብቻ የሚፈትነኝ?
የማልችለውን በዛ ላይ በጣም ከእኔ አቅም በላይ የሆነ ፈተና ለምን ያመጣብኛል?

ሌሎች በስላም እየኖሩ ሁል ጊዜ እኔን ፈተና አያጣኝም እያልን እናማርራለን።

እስቲ ከላይ የተጠቀሰውን ጥቅስ ልብ ብለን እንይ
ይህን ጥቅስ ስናይ ብዙ ነገሮችን እንረዳለን።

ለሰው ሁሉ ከሚሆን በቀር ምንም ፈተና አልደረሰባችሁም ይላል። ይህ ማለት ማንም ሰው እንደሚፈተነው ሁሉ እኛም ተፈተንን እንጂ ፈጣሪ እያዳላ አንዱ ላይ ፈተና እያዘዘ ሌላኛውን የማይፈትን አይደለም ሁላችንም ልጁ ነን ጌታ ለሁሉ እኩል ነው የእንጀራ አባት የሆነለት ሰው የለም ስለዚህ እኛን ብቻ ለይቶም እንደሚፈትን አድርገን መቁጠር የለብንም።

ነገር ግን ከሚቻላችሁ መጠን ይልቅ ትፈተኑ ዘንድ የማይፈቅድ እግዚአብሔር የታመነ ነው። ይላል እዚህ ጋር የምናየው ሁላችንም በአቅማችን ልክ እንደምንፈተን ነው። ግለሰቡ ከሚችለው በላይ ፈተና አይታዘዝበትም በትንሽ ፈተና የምንሰበር ሰነፎች ከሆንን አንደ እዮብ ሚስት እግዚአብሔርን ለመሳደብ ይቃጣናል ማለት ነው። ጠንካሮች ከሆንን ደግሞ እንደ እዮብ እስከመጨረሻ እንፀናለን። ልብ በሉ ጥንካሬአችን በበዛ ቁጥር ፈተናችንም በዛው መጠን እየጨመረ ይመጣል አንድ ክፍል ገብቶ ተፈትኖ ያለፈ ተማሪ ለቀጣዩ ፈተና እራሱን ማዘጋጀት አለበት ክፍል እየጨመረ በመጣ ቁጥር ፈተናውም እየጠነከረ ይመጣል ማለት ነው ጎበዙን ከሰነፍ ለመለየት ፈተና የግድ ነው።

ትታገሱም ዘንድ እንድትችሉ ...
የትእግስታችንን ደረጃ ወይም አቅም ለመለካት እንደምንፈተን ይናገራል።
እግዚአብሔር ምን ያህል ጠንካራ እና ብርቱ እንደሆንን ለማወቅ በተለያየ አጋጣሚ የተለያየ መሰናክሎችን እያመጣ ይፈትነናል ነገር ግን እኛን ብርቱዎች እና ጠንካሮች ለማድረግ እንጂ እሱ ባመጣብን መሰናክል ተደናቅፈን ወድቀን እንድንቀር አይደለም።

ከፈተናው ጋር መውጫን ደግሞ ያደርግላችኋል።
ይህ ማለት ሁሉም ሰው አቅሙ እስከቻለው ድረስ ተፈትኖ ስያበቃና መድከሙ ሲታይ አቅሙ ምን ያህል እንደሆነ በትክክል ከተረጋገጠ ቦሀላ ከዛ ፈተና እንዴት መውጣት እንደሚችል ጌታ ዘዴ ይሰጠዋል ማለት ነው።
እስቲ ማነው ወደፈተና ገብቶ በራሱ ሀይል ከገባበት ፈተና መውጣት የሚችል? እንደውም በእራሳችን መንገድ ከፈተናዎቻችን ለመውጣት ጥረት ማድረግ ስንጀምር ነገሮች የባሱ ይሆናሉ። እንደውም ጭራሽ የማንችለው ፈተና ይጨመርብናል። ነገር ግን ይህን ፈተና እኔ አልቻልኩም ከእኔ አቅም በላይ ነው ብለን ተደፍተን ብናነባ እና የከበደንን በጌታችን ፍት ጥለን አንተ እወቅልኝ ብንለው ከአቅማችን በላይ እንድንፈተን ስለማይፈልግ ፈጥኖ ሸክማችንን ያቀልልናል።

ፀሎት
አምላኬ ሆይ እኔ ደካማ ፍጡር በመሆኔ በገባሁባቸው ፈተናዎች ሁሉ እያማረርኩ አንተን አሳዝኜሀለሁ። አንተ በእኔ ላይ ያለክ አላማ ፍቅር እንደሆነ ተረድቻለሁ። የምፈተነውም ለመልካም እንጂ ለውድቀት ስላልሆነ ለፈተናዎች ሁሉ እጄን እንዳልሰጥ አንተ አበርታኝ።
መውጫ ቀዳዳም እየሰጠህኝ የምስጋና ሰው አድርገኝ።
በኢየሱስ ስም አሜን።

@MARANATHAWOCH
@MARANATHAWOCH

የመወያያ ግሩፕ @marantawoch
423 views15:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ