ፍቅር ስለሚጠይቀው መስዋእትነት ካህሊል ጂብራን የፃፈውን ውብ እና ነፍስን የሚማርክ ፁሁፍ ልጋብዛችው " ፍቅር በዓይኑ ጥቅሻ በጠራችሁ ጊዜ መንገዶቹ ምን ያህል አስቸጋሪ እና አቀበት ቢሆኑም ተከተሉት...ክንፎቹ ሲያቅፏችሁም ተሸጎጡበት ። በላባዎቹ መሀል የተደበቁ ሰይፎች ቢያቆስሏችሁም ወደኋላ አታፈግፍጉ ... ፧ ሲያነጋግራችሁም እመኑት ። ድምፁ የሰሜን ኃይለኛ ንፋስ የአትክልትን ስፍራ እንደሚያወድም ሁሉ ህልሞቻችሁን ቢበታትንባችሁም እሱን ከማመን አታመንቱ.. ፍቅር ዘውድ የሚደፋላችሁን ያህል ይሰቅላችሁም ይሆናል ። የሚያሳድጋችሁንም ያህል ይከረክማችኋልም...እስከ ጫፍ ከፍ ብሎ በፀሃይ ውስጥ የሚወዛወዙትን እጅግ ለስላሳ ቅርንጫፎቻችሁን በፍቅር እንደሚደባብስ ሁሉ ፣ በመሬት ውስጥ ቁልቁል ወደ ስሮቻችሁ ወርዶም ተጠምጥሞ ከመሰረታቸው ይነቀንቃቸዋል.. እንደ በቆሎ ክምር ወደ ራሱ ይሰበስባችኋል ። እርቃናችሁን ሊያስቀራችሁም ይወቃችኋል ። ከላፋችሁ ሊያላቅቃችሁም ይነፋችኋል ። ነጭ ዱቄት እስክትሆኑም ድረስ ይፈጫችኋል ። እስክትለወጡም ያቦካችኋል ። ከዚያ ለአምላክ ቅዱስ ድግስ የምትቆረሱ ቅዱስ ዳቦዎች ትሆኑ ዘንድ ወደ ተቀደሰው እሳቱ ውስጥ ይጨምራችኋል.... ፍቅር እነዚህን ሁሉ ነገሮች የሚያደርግባችሁ ፣ የልባችሁን ምስጢራት እንድታውቁ እና በዚያ ዕውቀትም የህይወት ልብ አንድ ግማድ እንድትሆኑ ነው... ፧ ይሁንና ፍርሃት አድሮባችሁ የፍቅርን ሰላም እና የፍቅርን ደስታ ብቻ የምትሹ ከሆነ፣ እርቃናችሁን ሸፍናችሁ ከፍቅር የመውቂያ ውድማ ወጥታችሁ ብትሄዱ ይሻላችኋል ። ወደዚያ የሄዳችሁበት ወቅቶች የማይፈራረቁበት ወቅት - አልባ ዓለም ውስጥም ትስቃላችሁ ። ነገር ግን ሳቃችሁን ሁሉ አትስቁትም ። ታላቅሳላችሁም፤ ግን እንባችሁን ሁሉ አታፈሱትም:: ደራሲ ካህሊል ጂብራን ከንባብ ዳርቻ ለህይወት ጠአም!! #share and #join for more @KenibabDaricha @KenibabDaricha 1.2K views€£phâ (SânTos), 19:34