Get Mystery Box with random crypto!

🌀የሀበሻ ዑለማዎች🌀

የቴሌግራም ቻናል አርማ ye_habesha_ulmoch — 🌀የሀበሻ ዑለማዎች🌀 የ
የቴሌግራም ቻናል አርማ ye_habesha_ulmoch — 🌀የሀበሻ ዑለማዎች🌀
የሰርጥ አድራሻ: @ye_habesha_ulmoch
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.42K
የሰርጥ መግለጫ

🍬🍬በዐሪፎች ጀሰድ ላይ ተጠምጥማ፣◆🍬
◍🍬◍ በሷ እያዜሙ ስንቱ ሰው ደማ፣🍬◍🍬
🍬◍ልቤን ወሰደች እቺ መንዙማ፣🍬◍🍬
ⓂⓂⓂⓂⓂⓂⓂⓂⓂⓂⓂⓂⓂⓂ
👳 የቀደምትና አሁን ላይ ያሉ ኡለማዎች መንዙማዎቻቸውና ስራዎቻቸው የሚቀርብበት ቻናል ነው ።

Ratings & Reviews

4.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-06-12 17:29:32 ሼህ ወረ-ዋዩ [ ሼህ አደም ኢብኑ ዮሱፍ ]
➀➇➅⓪-➀➈➄➁ ዓ/ኢት ያረፉ
ወረ-ዋዩ-ባቲ!
-- --
┊┊┊┊┊ 
┊┊┊┊
 ┊┊┊
┊┊
┊

.................................
ደግሞ ተዋዱዑ ኣጃኢበል ቁድራ፣
በነ ሲራጅ ጓጉር፣ ባአባ ስበር ሐድራ፣
ደግሞ በሰ'ተዋ፣ አጓዘ ለቂድራ፣
ለጥቆ ቀልቀሻ፣ ቀድጨራ ሞጨራ፣
ጧ'ዓን ለብሷት ነበር፣ ታጅ አድርጎ ጡሩራ፣
ሰርቶ በማሰራት፣ ለግሶ ፈይድሁ፤
ጌታዬ እንዴት ነሁ? ምን ነው ባየነሁ!
አላሁመ ሶሊ አላ ሙሀመድ (2)
ጌታዬ እንዴት ነሁ ምነው ባየነሁ!
( ማዲህ፦ ሼህ ሙሀመድ አወል ሃምዛ )
፧
፧
..........
የህይወትና የሠውነት አስኳል ናት፣ ሀገር-አብቂ፣ ትውልድ-አፍላቂ አሻራዎችን አኑራለች፣ መልካምነትን አስቆጣሪ ትሩፋቶች ይመነጩባታል ፣ማዕከለ-ዉበት፣ ማህሌተ ኃይማኖት፣ የብዙ ገናኖች መፍለቂያ <ባቲ>! በወጉ ታሽተው ያልተዳሰሱ እና እንደሚገባቸው ያልተወሱ ኢስላማዊ ትውፊቶችን አቁታ አኑራለች፡፡ ይህን አካለ-ኢስላማዊ ታሪኳን ስታስመለክትም፣ አያሌ የኃይማኖቱን ሊቃውንታት አያይዛ ታስገመግማለች ።‹ሰ'ተዋ› ከ‹ሀ'ዶ› ሀሪማ ብዙ ባልራቀ መልኩ ይገኛል:ሀሪማን ደጋግመዉ ረግጠዋል። ልሳነ-ፈርጣማው የጫሊው ሼህ (ሰኢድ እብራሂም 1872-1947) ፍሬያቸው አኩርቶ፣ ዘራቸው አፍርቶ፣ የደም ጠብታቸው ጎልቶ ይታወስና ይቀጥል ዘንድ ለልጃቸው 'ቱፍታ'ን ከጅለዉ፤ ልጃቸዉን ሼህ (ሙሃመድ መኪን)ን ይዘዉ መቅናቸዉ እስኪፈስና እግራቸዉ እስኪዝል ሰ'ተዋን ዙረዉበታል።
.................
ዳሩ አሁንም ማዕዱ አልረገበም፣ በረከቱ አልደረቀም፣ የዕውቀትን ሥልጣኔ ሳያጎድሉ፣ መንፈሳዊ ዝማሬም በወጀብ ሳይገታ፣ ሼህ ወረ-ዋዩ በልጃቸው በ[<ሼህ አብዱል-ዉሃብ ሼህ> ተተክተዋል፤ የዘመን ጸሐይ ናቸው፣ የዒልም አክሊልን ደፍተው፣ አርቅቆ ተናጋሪነትን ተላብስዉ፣ ምጡቅ ጸሐፊነት ተክነዉ፣ በገናን ገጣሚና ድምፀኛነት ብቅ ያሉ ናቸው፤ <መርከበል-አህባብ> የተሰኘ ክትብ(መጸሃፍት) ለዓይነ-ሥጋችን አብቅተዋል። ስለ ሼህ <አብዱል-ዉሃብ ሼህ> አላህ ፍቃዱ ከሆነ ወደ ፊት በሰፊው እንከትባለን]፡፡
....................
እነ ሼህ ወረዋዩ ያልተዛነፈ ሰብዕናን ለመጭዎች አትርፈዋል፣ የእኛ ምንዳ፣ የልባችን ማረፊያ እና ሁለመናችንም ሆነው ይታያሉ፣ ይታወሳሉ። ሸክም በማይጠላ ትካሻቸው፣ ብሶት ባላጎበጠው ጫንቃቸው፣ ትውልዳንን እንዳዘሉ አመርቂ ሊቃውንት፣ አብቃቂ ዒልም እና አንጋሽ ሰብዕናን የዘሩ ሆነው በ1952 በወርሃ-ሰኔ /ዙልሂጃ/ቀን18 ዕለተ-ረቡዕ በ92 አመታቸው ምድርን ተሰናብተዋል።
ድብቁ-ንጉሥ!!!
፧
۝ رحمه الله على شَيْخِنَا وَأُسْتَاذُنَا اجعل قبره روضةً من رياض الجنّة، وَجَمِيْع الْأوْلِيَآء، وَوَالِدَيْهِم وَمَشَايخِهِم وَزُرِّيَّاتِهِم وَخُلَفَائِهِم وَآتْبَاعِهِم، وَسَائِرِ مَنْ لَهُ عَلَيْنَا امدد لَهُمْ الْفَاتِحَة ۝
┄┄┉┉✽‌»‌ أمين »‌✽‌┉┉┄┄
(ፎቶ፦በቅርብ ዘመን የታደሰው የሼይኽ ወረ-ዋዩ ሀሪማ-ሰተ'ዋ)
፧
ምንጭ
. "ኢዕላሙል አግቢያዕ ቢሃያቲ ዑዞማዑ ኢትዮጵያ" ገጽ-56; በሼህ ሙሃመድ ታጁዲን
. "ተውሱላት" በሼህ ሙሀመድ ሼህ/ቢላ-ገርፋ
. " ኢቃዙል ሂመሙል አግቢያዕ" በሀጅ ሙሀመድ-ወሌ
ከቃለ መጠይቅ።

በዚህ ቻናል
ስለ ወርቃማው ታሪካችን እናወራለን።
ዑለሞቻችንን እናወሳለን፤
ጀግኖቻችንን እንዘክራለን፤
ሳይንቲስቶቻችንን እናነሳለን።

ለመቀላቀል ይህን ይጫኑ

ሟር ሟር
@ye_habesha_ulmoch
@ye_habesha_ulmoch
@ye_habesha_ulmoch
793 views14:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-02 18:10:52
ከሚስ ሙባረክ
786 views15:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-02 18:09:13 "እባክህ አሳምረው ኸልቁን አታስቸግረው ኸይር እንዲሰራ እዚሁ ሙሀመዱ ረሱሉሁ" ይለዋል ማዲሁ።መቼም በኒ አደም እስትንፍሱ በዱንያ ላይ እስካለች ድረስ ኢማኑ በፀጉሩ ልክ በቀጠነች ቁጥር ወንጀል የመስራት አባዜ የጠናወተዋል ። ባንድ ወቅት አንድ ወጣት ሀጢያት ይሰራ ዘንድ ለማስፈቀድ ወደ አንድ ታላቅ አሊም ሄዶ ጠየቃቸው ።አሊሙም አላህን አትፈራም እንዴት እንዲህ ተብሎ ይጠየቃል ብለው እኛ ልንመልስለት በምንችለው መንገድ ሊያስረዱት አልወደዱም ። ነገር ግን ጥበብ የተሞላው መልሳቸውን አስደገፉት። "አዎ በአላህ ላይ መወንጀል ትችላለህ ነገር ግን መስፈርቶች አሉት እሱም የምትሰራው ወንጅል አላህ በፈጠረው ምድር መሆን የለበትም ምክንያቱም እሱን የሚያስከፍው ወንጀልህ በገዛ መሬቱ ላይ አሱን ማመፅ ስለሌለብህ " አሉት። ወጣቱም "እነ ሸህ ምድር ሁሉ የአላህ ሁና ሳለ ወዴት መሄድ ይቻላል"ሲል ሸሆቹም"እንግዲያውስ በገዛ ምድሩ ላየ ሆነህ እሱን ስታምፅ ትንሽ አታፈርምን ? የግድ መወንጀል እሻለው ካልክ በግራ እና በቀኝ ላሉት መላይኮች አንዴ ወንጀል እስክሰራ ድረስ ተዉኝ እና ተመልሳቹ ኑ በላቸው" ወጣቱም "አየቀለዱብኝ ነው" ቢላቸው አንተ ነህ ቀልዱን የጀመርከው ብለውት አረፉ ። እናም ያ ጀመአ ከምንተነፍሰው የማዕስያ ትንፍሽ ተላቀን ከሳሊሆቹ ቅፍለት ተርታ ለመሰለፍ እንሩጥ ። አሪፎቹ እንዳሉት " ያለፈህን ለማካካስ እሩጥ ባይሆን በወንጀል የወፈረ ስብዕናህን ወንጀል በማቆም አቅጥነው በዚህ ውፍረትህ የምትፈልገውን ያክል መሮጥ አትችልም እና" ይላሉ ። አቦ ከአሪፎቹ ተርታ አላህ ያሰልፈን ።
በዚህ ቻናል
ስለ ወርቃማው ታሪካችን እናወራለን።
ዑለሞቻችንን እናወሳለን፤
ጀግኖቻችንን እንዘክራለን፤
ሳይንቲስቶቻችንን እናነሳለን።

ለመቀላቀል ይህን ይጫኑ

ሟር ሟር
@ye_habesha_ulmoch
@ye_habesha_ulmoch
@ye_habesha_ulmoch
725 viewsedited  15:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-04 18:35:32 ሙላው ያገሬ ህዝብ የሚያቃቸው "የመርሳው አባ ጌትዬ"በሚለው መጠርያ ነው ። በዱንያ ላይ ረጅም አመት ከቆዩ አሊሞች ተርታ ይመደባሉ ።ሸህ መሀመድ ሚዕዋ ።

አላህ የሰጣቸው ወልይነታቸው ነጥሮ ይነገርላቸዋል ።እሳቸውን የዘየረ ሀብታም ሆነ ደሀ ሹምም ይሁን ተራ ሰው የሂወቱን ስንክሳር በአላህ ፍቃድ ሳይነገረው አይመለስም ነበር።
በውስጡ ሸር ያዘለውን ገልጠው ሸሩን ጠርገው በምክር ገስፀው ይመልሱታል ።

እኚህ አራት አይና የኢስላም ሊቅ ብዙ ያልተነገሩ ጉድ ያዘሉ ሚስጥሮችን በሂወታቸው ዙሪያ ይነገራል ። "የውኃላው ከሌለ የለም የፊቱ እንዳለው ቴዳ" የፊቱ እንዲረጋ የውኃላውን በወፍ በረር እነሆ ።

መንግስቱ ኃይለማርያም በ1974 ዓ.ል ከመቅደላ ለጉብኝት ሲመለሱ ለመጀመርያ ጌዜ እንደዘየሩዋቸው ይነገራል ።
ሸሆቹም "መቼም ወሎን ንጉስ መቶ ውሎ አደረባት ማለትን ሰምተን አናውቅም እና ላንተ ሶስት ቀን ውለህ እንድታድር ከአላህ ተፈቅዶልሀል" ሲሉዋቸው በደሴ መርሆ ቤተ መንግስት ሶስት ቀን ሊቆዩ ችለዋል ።

1980 መንግስቱ ለሁለተኛ ግዜ ሂደው ዘይረዋቸዋል ። በጊዜው የነበረው የፖለቲካ ውጥረት ስርአቱ አጣብቂኝ ፈተና ውስጥ እንደመግባቱ ለመፈረጅ በሚመስል መልኩ "ምን ይሻላል "የሚል ጥያቄ አቅርበውላቸው ከመርሳው ጌታ ምላሽ አግኝተዋል ።
"ግንቦት የሚሉት ወር ባንተ ላይ ሊጠመጠም አሰፍስፎዋል የምትመጣዋ ግንቦት እንኩዋን 1981 መላም የላት በራስዋ ገመድ ተጠልፍ ተዝለፍልፋ ትወድቃለች ።ላንተ የምታስፈራዋ የወዳኛዋ ግንቦት ናት 1983 ።ባልንጀሮችህ እንደ ከብት በረት ይማቅቃሉ ።አንተም ሀገር እና ወገን እንደናፈክ ትቀራለህ አብሽር የምትሆነው ነገር የለም ለአላህ ነግረን እናስመልጥሀለን "በማለት ፈርደዋል ።

በነገራችን ላይ ይህንኑ ታሪክ ባልሳሳት ከሶስት ወይም ከአራት አመት በፊት በሪፖርተር ይሁን አዲስ አድማስ ጋዜጣ ላይ በፊለፊት ገፁ የመንግስቱ ሀይለማሪያም እና የሸህ መሀመድ ሚዕዋ ያልተነገሩ ሚስጥሮች በሚል ርዕስ ለህዝብ ለንባብ ማብቃቱን አስታውሳለው ።እንዲሁም በሸገር ሼልፍ በሰፊው ተተርኩዋል። ተስፍዬ ብርሀኑ የተባለ ደራሲ አራት አይና በሚል ባሳተመው መፀሀፍ ሌሎች ታሪኮችን ጨምሮ ያወሳዋል ።

እኚህ የሸረፍ ካባ የለበሱ ታላቅ አሊም የመሞቻ ቀናቸውን ሳይቀር ቀደም ቡለው ነሀሴ 1ብለው ተናግረው ነበር ።እንዳሉትም በዛው ቀን ወደ አኬራ ተሻግረዋል ።
ነብይ ባገሩ ነው እና ተረቱ እኛም ለነሱ የሚገባቸውን ክብር እየሰጠን ታሪካችንን በማወቅና በማሳወቅ ረገድ ብንጥር መልካም ነው ባይ ነኝ ።
ፈገግ ያለች ጁምአ ትሁናላችሁ።
በዚህ ቻናል
ስለ ወርቃማው ታሪካችን እናወራለን።
ዑለሞቻችንን እናወሳለን፤
ጀግኖቻችንን እንዘክራለን፤
ሳይንቲስቶቻችንን እናነሳለን።

ለመቀላቀል ይህን ይጫኑ

ሟር ሟር
@ye_habesha_ulmoch
@ye_habesha_ulmoch
@ye_habesha_ulmoch
1.8K views15:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-17 13:29:10 ሰይዱል ዓሪፊን ሰይዱና ኑር ሁሰይን ባሌ
========= ============
*
ብርሀናማ ጨረቃ በጀማዱል ሳኒ አጋማሽ ላይ ስትዘልቅ… ከወደ ባሌ አናጂና ደማቅ የአሺቆች መዐድ ይኖራል… ግለገለ ጎበና መውሊድ...
*
ሰባት ክፍለ ዘመናትን የኋሊት መለስ ብለን ስንቃኝ ከታሪክ ብራና ላይ ይሄንን በወርቃማ ቀለም ተከትቦ እናገኛለን... ከገውሱል አዕዞም ... ሰይድ ዐብዱልቃዲር አል-ጀይላኒ መድረሳ ምሩቅ የሆኑ 405 ተማሪዎች በሸይኽ አባዲር እየተመሩ ወደ ጥንታዊቷ ሀረር ከተማ ይዘልቃሉ ...በዚህ እንቁ ስብስብ ውስጥ ሸይኽ ኢብራሂም የተባሉ ፈርጥ ነበሩበት...
*
ሸይኽ ኢብራሂም... ቁረይሺይ ናቸው፣ የዘር ሀረጋቸው ከአቂል ቢን አቡጧሊብ ይመዘዛል... ይህም አህለልበይት ያደርጋቸዋል ... የኋላ ኋላ ከወደ ባሌ አናጂና ቀበሌ ዘልቀው እመት ማኪዳ ጋር በትዳር ይጣመራሉ... መልካም ፍሬዎችንም ያፈራሉ... የሀበሻውን የብርሃነ ቀንዲል ተወዳጁ ልዑልም ከፍሬዎቻቸው መካከል ናቸው...
*
ሸይኹ ሰቀለይን... ቁጥቡል ሀበሻ ... ሰይዱል ዓሪፊን ሰይዱና ኑር ሁሰይን ባሌ … አቢዮ በመባል ይታወቃሉ... ከ400 አመታት በላይ በህይወት እንደኖሩ ተዘግቧል ... ሀበሻን በማቅናት ወደርየለሽ ገድል ፈፀመዋል... ሰለእርሳቸው የህይወት ታሪክ አያሌ ምሁራን ጥልቅ ጥናት አድርገዋል... ግለ ታሪካቸው "ረቢዐል ቁሉብ" ደግሞ ከመሻኢኾቻችን ዘንድ እጅግ ውዱ ንብረት፣ የተከበረው ካዝናቸው ነው... አንድ ውብ ንግግራቸውን ለናሙና …
*
«ድር ፤ ለሸረሪት ብቸኛ መንገዷ ብቻ ሳይሆን ሌላን የማያስጉዝ ጭምርም ነው... ቦይም ዉሃን'ንጂ ሌላን አያሳልፍም ... ውሃውም ያለ ቦይ ሲፈስ አጥፊ ነው ... ልክ እንዲሁ የአዋቂዎች መንገድም አዋቂዎችን ብቻ የሚያስጉዝ ነዉ»
ሰይዱና ኑር ሁሰይን ባሌ (ق)
Thamer Nur

* * * * * * * * * ** * * * * * * * * *
አሏሁ መርሃም ኑር ሁሰይን
አሏሁ መርሃም ኑር ሁሰይን
ሸፊዑል ወራ ፊዳረይን

==================
*
ኑር ሁሰይን ቁጥቡል ሀበሻ
የአይታም ምስኪን መሸሻ
የታረዘውን መልበሻ
አሽራር በላዕ መመለሻ
ማበሻ ሲቃ ሀዘኔን
ሸፊዑል ወራ ፊዳረይን...
*
ኑር ሁሰይን የከውኑ አባት
ዙህድ ነው የሱ ሚለት
ፆም ውሎ ያድራል ሶላት
ላጣው እናት ነው አባት
ለሰው ለእንስሳ አሳቢ
ሸፊዑል ወራ ፊዳረይን...
*
በአናጂናው ሰፈር
ይፋ ወጥቷል ያንቱ ሲር
አያልቀው ሲመነዘር
እንደው ገና በኸበር
ላቤን ቆረጠልኝ ጥሜን
ሸፊዑል ወራ ፊዳረይን...
*
ከቁረይሽ የሆነው ዘሩ
ሲወለድ የታየው ኑሩ
አዛኝ ለምስኪን ፈቂሩ
ደርሶ ተበልቷል ሰመሩ
ተከውኑ ዋርካ ኑር ሁሰይን
ሸፊዑል ወራ ፊዳረይን...
*
ሰላም አለይኩም ነጋሲ
ሰላም አለይኩም አባባ
ገሩ ኢላላ ዱቢኒ
ዬ ገሪፍ ገሌ መሌ
ኬሰን ሒክማዳ ዱቢኒ
አሏሁ መርሃም ኑር ሁሰይን
* * * * * * * * * *


አሏሁ መርሃም ኑር ሁሰይን
ሸፊዑል ወራ ፊዳረይን
አሏሁ መርሃም ኑር ሁሰይን
ሸፊዑል ወራ ፊዳረይን
*
ኑር ሁሰይን የአላህ ገበር
የአውልዬቹ ስመጥር
ከራማው ላይቆጠር
አንጠፈጠፈው ቀለሜን
*
ኑር ሁሰይን የሌት ንጋቱ
ድልቡን ተግቶት በጠዋቱ
ፈሰሰ ብትከጅሉ አንቱ
ከታች ወደ ላይ ጅረቱ
*
ምላሱ ኢልምን ያንቧቧል
አይኑ ለጌታው ያነባል
ሌላን አጥግቦ ይራባል
ያስባል ዳኢም ለከውነይን
*
ደማም የደማም ወለድ - ቁረይሺይ ናቸው
የነቢ ቤተሰብ - ከአቂል ነው ዘራቸው
በመሪነት ሰም ወርቅ - ቢቀኘው ኑራቸው
የሰቀለይን ሼህ - ነበር ስያሜያቸው

#አቢዬ_አቢዬ_አባኮ_ኑር_ሁሰይን!!!
Fuad Yasin

በዚህ ቻናል
ስለ ወርቃማው ታሪካችን እናወራለን።
ዑለሞቻችንን እናወሳለን፤
ጀግኖቻችንን እንዘክራለን፤
ሳይንቲስቶቻችንን እናነሳለን።

ለመቀላቀል ይህን ይጫኑ

ሟር ሟር
@ye_habesha_ulmoch
@ye_habesha_ulmoch
@ye_habesha_ulmoch
1.7K views10:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-13 16:18:28 ሙጃሒድ ሰይድ ሙሐመደ ሻፊ
========================

ሙጃሒድ ሰይድ ሙሐመደ ሻፊ(ቀ) እንደሚታወቀው ብዙ ጀሀድ አድርገዋል:: በስተመጨረሻ ቱርኮች (Ottoman Empire) የሀረርን ግዛት በቁጥጥራቸው ስር አድርገው ያስተዳድሩ በነበረበት ወቅት… ሰይድ ሙሐመድ ሻፊ ጀሐድ ላይ መሆናቸውን የሀረሩ አስተዳዳሪ ሲሰማ የተወሰኑ መድፎችን እንዲዋጉበት ይልክላቸዋል... በዛን ወቅት የወሎው ንጉስ ራስ አሊ ደግሞ ከጎንደሩ ንጉስ ጋር ጦርነት ላይ ነበር... ሰይድ ሙሐመድ ሻፊ የተላከላቸውን መሳሪያ ከተቀበሉ በሁዋላ ለወሎው ንጉስ ራስ አሊ እንዲህ አይነት መሳሪያ መጥቶልኛል... አንተ ንጉስ ነህና ከሚዋጉህ ጠላቶችህ ተዋጋበት ብለው ይሰጡታል

መሳሪያውን ከሰጡት በሁዋላ ራስ አሊ ከጎንደሩ ንጉስ እርቅ ያወርድና ሰይድ ሙሐመድ ሻፊ(ቀ) የሰጡትን መሳሪያ ጠላታቸው ለሆነው ለጎንደሩ ንጉስ ያስረክባል ያኔ ስይድ ሙሐመድ ሻፊ ይደነግጣሉ... ራስ አሊ ከድቶኝ በጦር ይወጋኝ ከነበረው የጎንደር ንጉስ ጋር ታርቋል... ስለዚህ ከአሁን በሁዋላ ይሄ አገር አያስቀምጠኝም በማለት ወደ መዲና ይሰደዳሉ... መዲና ላይ ለ ሁለት አመታት ያክል ይቆያሉ...

አብሬትዩ ሳኒ(ቀ)እንደተናገሩት ሰይድ ሙሐመድ ሻፊ(ቀ) መዲና ላይ ሁለት አመታት ሲቆዩ ለአንድ ሰአት ያክል እንኳን ከ አሽረፈል ኸልቅ ﷺ ጋር ሳይለያዩ ነበር የቆዩት... ከሁለት አመት ቆይታቸው በሁዋላ ሙሐመድ ሻፊ ሆይ ተነስ ወደ ሀገርህ ግባ ብለው አሏቸው ሰይደል ዉጁድ ﷺ እሳቸውም ያረሱለሏህ ﷺ በዚህ... በዚህ.. ሰበብ ነው ሀገሬን ጥዬ የወጣሁት ሀገሬ መግባት አልችልም ብልው ሲሏቸው ነብዩም ﷺ አብሽር ምንም አትሆንም ግባ ነገር ግን ከአሁን በሁዋላ እዋጋለው ብልህ እንዳትወጣ... ጀሀድህን ሀድራህ ውስጥ በሙሰላህ ላይ አድርገው... ከመሄድህ በፊት እንዲህ.. እንዲህ.. ቦታ ላይ ዋሻ አለ ዋሻው ውስጥ የዘመኑ ቁጥብ አለ እሱን ዘይረህ ወደ ሀገርህ ሂድ ብለው አሏችው::

ነብዩ ﷺ ባሉዋቸው መሰረት ወደ ሀገራቸው ጀማ ንጉስ ገቡ... የጎንደሩ ንጉስ እና ራስ አሊ የሰይድ ሙሀመድ ሻፊን(ቀ) መግባት ሲሰሙ ሊይዟቸው ወደ ጀማ ንጉስ ያቀናሉ... ጀማ ንጉስ ሊደርሱ የሁለት ቀናት ያክል መንገድ ሲቀራቸው ወደ ጀማ ንጉስ ጭራሽ የማይታይ ጨለማ ይሆናል.. ነገሩ ምንድነው ብለው ሲያጤኑ የጨለመው እሳቸው ከገቡ በሁዋላ መሆኑን ይረዳሉ.. እዛው የሚኖር ሰላማዊ ሰው መርጠው ሲልኩ በሰላም ገብቶ ይወጣል ለእነሱ እና ጦራቸው ግን ምንም የማይታይ ጨለማ ይሆናል...

ያኔ እርቅ እናውርድ ብለው ከጀማ ንጉስ ጋር ይደራደራሉ... ከመስጂዳቸው ዙሪያ 40 ጋሻ መሬት ለምንግስት የማይገብር የሳቸውን ሀድራ ብቻ የሚሀድም የሆነ ነገር ይሰጧቸዋል... ሰይድ ሙሐመድ ሻፊም ይህንን መሬት ተቀበሉ... ቀጥሎም በሸይኻቸው ሰይድ ፈቂህ ዙበይር የቃዲርያ ጦሪቃ ኸሊፋ ሆነው ተኸለፉ... በሀገራችን የሀድራ ስራን በሰፊው አስፋፉ...

አብሬትዩ ሳኒ(ቀ) በዋእዛቸው እንደተናገሩት የጀማ ንጉስ ሀድራ እና የአብሬት ሀድራ ምንም ሳይቀዘቅዙ እየደመቁ እስከመጨረሻ የሚቆዩ ሐድራዎች ናቸው ብለዋል

#ሺሊላ_ሺሊላ_ሰይድ_ሙሀመድ_ሻፊ
#ኸበሩኩም_ደዋ_ዊዳዱኩም_ሻፊ

ምንጭ አብሬትዩ ሳሊስ ሸይህ ሰይድ ሚቅባሰል ኑር ሐፊዘሁሏህ
ሺሊላቱ አብሬትዩ ሳኒ ሰይድ ሙሐመድ ሻፊን ያወደሱበት መድህ መሽረብ ነው

በዚህ ቻናል
ስለ ወርቃማው ታሪካችን እናወራለን።
ዑለሞቻችንን እናወሳለን፤
ጀግኖቻችንን እንዘክራለን፤
ሳይንቲስቶቻችንን እናነሳለን።

ለመቀላቀል ይህን ይጫኑ

ሟር ሟር
@ye_habesha_ulmoch
@ye_habesha_ulmoch
@ye_habesha_ulmoch
1.4K views13:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-07 17:37:21 عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم صلى الله عليه وسلم
ውዶቼ ጁምአ ሙባረክ
ሰለዋት እናብዛ روحنا بالقرآن
ቁርኣን የመንፈሳችን የአካላችን እና የሕይወታችን መመሪያ እና ዘመን የማይሽረው መድሐኒት ነው!

ምርጥ የቴሌግራም ቻናል ነው ይቀላቀሉ
ለመቀላቀል ይህን ይጫኑ
?
t.me/ye_habesha_ulmoch
t.me/ye_habesha_ulmoch
t.me/ye_habesha_ulmoch

ሟር ሟር
1.3K views14:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-11-25 12:29:04 መላው ያገሬ ህዝብ የሚያቃቸው "የመርሳው አባ ጌትዬ"በሚለው መጠርያ ነው ። በዱንያ
ላይ ረጅም አመት ከቆዩ አሊሞች ተርታ ይመደባሉ ።ሸህ መሀመድ ሚዕዋ ።
አላህ የሰጣቸው ወልይነታቸው ነጥሮ ይነገርላቸዋል ።እሳቸውን የዘየረ ሀብታም ሆነ ደሀ
ሹምም ይሁን ተራ ሰው የሂወቱን ስንክሳር በአላህ ፍቃድ ሳይነገረው አይመለስም ነበር።
በውስጡ ሸር ያዘለውን ገልጠው ሸሩን ጠርገው በምክር ገስፀው ይመልሱታል ።
እኚህ አራት አይና የኢስላም ሊቅ ብዙ ያልተነገሩ ጉድ ያዘሉ ሚስጥሮችን በሂወታቸው ዙሪያ
ይነገራል ። "የውኃላው ከሌለ የለም የፊቱ እንዳለው ቴዳ" የፊቱ እንዲረጋ የውኃላውን
በወፍ በረር እነሆ ።
መንግስቱ ኃይለማርያም በ1974 ዓ.ል ከመቅደላ ለጉብኝት ሲመለሱ ለመጀመርያ ጌዜ
እንደዘየሩዋቸው ይነገራል ።
ሸሆቹም "መቼም ወሎን ንጉስ መቶ ውሎ አደረባት ማለትን ሰምተን አናውቅም እና ላንተ
ሶስት ቀን ውለህ እንድታድር ከአላህ ተፈቅዶልሀል" ሲሉዋቸው በደሴ መርሆ ቤተ መንግስት
ሶስት ቀን ሊቆዩ ችለዋል ።
1980 መንግስቱ ለሁለተኛ ግዜ ሂደው ዘይረዋቸዋል ። በጊዜው የነበረው የፖለቲካ
ውጥረት ስርአቱ አጣብቂኝ ፈተና ውስጥ እንደመግባቱ ለመፈረጅ በሚመስል መልኩ "ምን
ይሻላል "የሚል ጥያቄ አቅርበውላቸው ከመርሳው ጌታ ምላሽ አግኝተዋል ።
"ግንቦት የሚሉት ወር ባንተ ላይ ሊጠመጠም አሰፍስፎዋል የምትመጣዋ ግንቦት እንኩዋን
1981 መላም የላት በራስዋ ገመድ ተጠልፍ ተዝለፍልፋ ትወድቃለች ።ላንተ የምታስፈራዋ
የወዳኛዋ ግንቦት ናት 1983 ።ባልንጀሮችህ እንደ ከብት በረት ይማቅቃሉ ።አንተም ሀገር እና
ወገን እንደናፈክ ትቀራለህ አብሽር የምትሆነው ነገር የለም ለአላህ ነግረን እናስመልጥሀለን
"በማለት ፈርደዋል ።
በነገራችን ላይ ይህንኑ ታሪክ ባልሳሳት ከሶስት ወይም ከአራት አመት በፊት በሪፖርተር ይሁን
አዲስ አድማስ ጋዜጣ ላይ በፊለፊት ገፁ የመንግስቱ ሀይለማሪያም እና የሸህ መሀመድ
ሚዕዋ ያልተነገሩ ሚስጥሮች በሚል ርዕስ ለህዝብ ለንባብ ማብቃቱን አስታውሳለው
።እንዲሁም በሸገር ሼልፍ በሰፊው ተተርኩዋል። ተስፍዬ ብርሀኑ የተባለ ደራሲ አራት አይና
በሚል ባሳተመው መፀሀፍ ሌሎች ታሪኮችን ጨምሮ ያወሳዋል ።
እኚህ የሸረፍ ካባ የለበሱ ታላቅ አሊም የመሞቻ ቀናቸውን ሳይቀር ቀደም ቡለው ነሀሴ
1ብለው ተናግረው ነበር ።እንዳሉትም በዛው ቀን ወደ አኬራ ተሻግረዋል ።
ነብይ ባገሩ ነው እና ተረቱ እኛም ለነሱ የሚገባቸውን ክብር እየሰጠን ታሪካችንን በማወቅና
በማሳወቅ ረገድ ብንጥር መልካም ነው ባይ ነኝ ።
መልካም ቀን(ከሚስ)
✦✦✦

በዚህ ቻናል
ስለ ወርቃማው ታሪካችን እናወራለን።
ዑለሞቻችንን እናወሳለን፤
ጀግኖቻችንን እንዘክራለን፤
ሳይንቲስቶቻችንን እናነሳለን።

ለመቀላቀል ይህን ይጫኑ

t.me/ye_habesha_ulmoch
t.me/ye_habesha_ulmoch
t.me/ye_habesha_ulmoch
ሟር ሟር
1.8K viewsedited  09:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-11-12 17:30:01
ኢና ሊላሂ ወኢነ ኢለይሂ ራጂኡን ቀብራቸውን ከኑር የባሰ ብርሀን ያድርግላቸው
1.7K views14:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ