Get Mystery Box with random crypto!

የአዋጅ ቃል📯

የቴሌግራም ቻናል አርማ yawajekale — የአዋጅ ቃል📯
የቴሌግራም ቻናል አርማ yawajekale — የአዋጅ ቃል📯
የሰርጥ አድራሻ: @yawajekale
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.82K
የሰርጥ መግለጫ

✥""እምነት ማለት ያላዩትን ማመን ነው ሽልማቱም ያላዩትን ማየት ነው። " /🏵ቅ.አውግስጢኖስ🏵/
"የምናየው የምናምነውን አይደለም የምናምነውም የምናየውን አይደለም (🏵ቅ.ዮሀንስ አፈወርቅ🏵)"" ✥▱
ለማንኛውም ሀሳብ @D27eyoab ይላኩልን

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-09-01 03:55:37 በ26 ታስበው የሚውሉ የመጀመሪያው የኢትዮጵያ ጳጳስ ፃድቁ አቡነ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን አቡነ ሀብተ ማርያም እንዲሁም ወላዴ አእላፍ አቡነ ኢየሱስ ሞዐ .....
እንኳን ለወርሃዊ በዓላቸው እንኳን አደረሳችሁ
ገድላቸውን እነሆ ለበረከት
436 viewsedited  00:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 03:53:31
421 views00:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 03:53:29
391 views00:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 03:53:27
388 views00:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 10:55:55
ለቅዱስ መርቆርዮስ ወርሃዊ በዓል እንኳን አደረሳችሁ
1.1K viewsedited  07:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 19:13:42 -6 ክንፍ አብቅለው
-የወርቅ ካባ ላንቃ ለብሰው
-ማዕጠንተ ወርቁን ይዘው
-ከ24ቱ ካህናተ ሰማይም ተደምረው
-ሥላሴን በአንድነቱና ሦስትነቱ ተመልክተው
-"ስብሐት ወክብር ለሥሉስ ቅዱስ ይደሉ" ብለው መንበረ ጸባኦትን አጥነው ወደ መሬት ተመልሰዋል::
*ተአምራት*
=>የተክልየ ተአምራት እንደ ሰማይ ከዋክብት የበዛ ነው::
*ሙት አንስተዋል
*ድውያንን ፈውሰዋል
*አጋንንትን አሳደዋል
*እሳትን ጨብጠዋል
*በክንፍ በረዋል
*ደመናን ዙፋን አድርገዋል::
+ብዙ ደቀ መዛሙርትን አፍርተው ደብረ ሊባኖስን መሥርተዋል:: በዚያም ሴትና ወንድ መነኮሳት እንደ ሕጻናት አብረው ኑረዋል:: በዘመናቸው ሰይጣን ታሥሯልና::
*ዕረፍት*
=>ጻድቅ: ሰማዕትና ሐዋርያ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ብርሃን ሆነው መከራን በብዙ ተቀብለው: እልፍ አእላፍ ፍሬን አፍርተው: በተወለዱ በ99 ዓመት: ከ8 ወር: ከ1 ቀናቸው ነሐሴ 24 ቀን በ1306 ዓ/ም ዐርፈዋል:: ጌታ: ድንግል ማርያምና ቅዱሳን ከሰማይ ወርደው ተቀብለዋቸዋል:: 10 ትውልድ የሚያስምር ቃል ኪዳንም ተቀብለዋል::
††† ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ †††
=>እጅግ የከበረችና የተመሰገነች እናታችን ቅድስት ክርስቶስ ሠምራን እናመሰግናታለን:: እርሷ በሁሉ ጐዳና ፍጹምነትን ያሳየች ኢትዮዽያዊት እናት ናት:: ገና ከልጅነት የነበራት የትሕትናና የመታዘዝ ሕይወት እጅግ ልዩ ነበር:: እናታችን ቅድስናን ያገኘችው ገና በትዳር ውስጥ እያለች ነው::
+ከተባረከ ትዳሯ 12 ልጆችን አፍርታ: ምጽዋትን የዕለት ተግባሯ አድርጋ ኑራለች:: በዚህ ደግነቷም ሙት እስከ ማንሳት ደርሳለች:: አብያተ ክርስቲያናትን አንጻ አንድ ልጇን (ዳግማዊ ቂርቆስን) አዝላ ምናኔ ወጥታልች::
+በደብረ ሊባኖስ ውስጥ የቆየችው ቅድስት እናት ተጋድሎዋን የፈጸመችው ግን ጣና ሐይቅ ውስጥ ነው:: በተለይ ለ22 ዓመታት ሐይቁ ውስጥ አካሏ አልቆ: አሣ በሰውነቷ ውስጥ እስከሚያልፍ ድረስ ተጋድላለች:: በቀኝና በግራ 12 ጦሮችን ተክላም ጸልያለች::
+ብዙ ኃጥአንን አማልዳ: 12 ክንፎችን አብቅላ: ከፍ ከፍ ብላለች:: ከርሕራሔዋ ብዛት የተነሳ ሰይጣንን እንኩዋ ለማስታረቅ ሞክራለች:: ጌታም ከሲዖል ነፍሳትን እንድታወጣ ፈቅዶላታል:: ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ያረፈችው በዚህ ዕለት ሲሆን አጽሟ ዛሬ በራሷ ገዳም (ጣና ዳር) ይገኛል::
+" ቅዱስ ቶማስ ዘመርዓስ "+
=>ቅዱስ ቶማስ "መርዓስ" በምትባል ሃገር የፈለቀ የንጋት ኮከብ: ጻድቅ: ገዳማዊ: ዻዻስ: ሐዋርያ: ሰማዕትና ሊቅ ነው:: የዚህን ቅዱስ ተጋድሎ እንደ እኔ ያለው ሰው አይቻለውም:: የእርሱ ሕይወት ክርስትና ምን እንደ ሆነ ያሳያል::
1.5K views16:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ