2022-08-31 16:40:48
“አቤቱ ወደ አንተ መልሰን እኛም እንመለሳለን፤ ዘመናችንን እንደ ቀድሞው አድስ፡፡” ሰቆ ኤር 5፡21
በኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን የአባዶ ሙሉ ወንጌል አጥቢያ
ከነሐሴ 30 - ጳግሜ 5/201 የጾምና የጸሎት ጊዜ
1ኛ) የምስጋና ጸሎት መዝ 136፡1-26
እንደዚህ በአንድነት እንድንጸልይ እድልን ስለተሰጠን ማመስገን
አንደ ግልም ሆነ ፤ እንደ ቤተክርስቲያን ፤ ስለሃገርም ጸልየን፤ ለምነን ፤ማልደን ፤ የሆነልንን ሁሉ እያሰብ ማመስገን
2ኛ) እውነተኛ ንስሃ ማድረግ መዝ 55፡ 7
ራሳችንን እየመረመርን ፤ስለቤተሰቦቻችን
ስለ ሃገር መሪዎች ፤ ፓለቲከኞች ምህረትን እንጠይቃለን
ስለ ባለስልጣናት፤
3ኛ) ምልጃ ከልመና ጋር መጸለይ 1ጢሞ 2፡1-2
ሰዎች እንዲድኑ፤ እግዚአብሔርን መፍራት በምድሪቱ እንዲሆን
የይቅርታ ህይወት እና እውነተኛ ፍቅርን መለማመድ እንድንችል፡፡
ለቃሉ ትኩረት የሚሰጥ ህይወት እንዲኖረን
ስለ ሃገራችን የሰላም ሁኔታ ስለ ምድሪቱ ኢኮኖሚ፤ ማህበራዊ ግንኙነት ፤ የሰዎችን መጥፎ የሆኑ አመለካከቶችን ሁሉ እግዚአብሔር እንዲቀይር
የታመሙ እንዲፈወሱ ፤ የተለያየ ችግር ስላለባቸው
በሱዳን፤ በግብጽ፤ በጎረቤት አገሮች ላይ እና በእነ አሜሪካ አውሮፓ መጸለይ
በቤተክርስቲያናችን የእግዚአብሔር
ሃይል እንዲገለጥ : ስለ ሪቫይቫል፤
ስለሃገራችን ሰላም ግጭትና ጦርነቱ ፤ ስደት እንዲቆም
ልጆችን አዳጊዎችን እና ወጣቶችን በእግዚአብሔር ፊት ይዞ መቅረብ
ስለ ተሰጠን ቦታ መጸለይ
4ኛ) እየተቃወምን መጸለይ ያዕ 4፡7
በግለሰብ ፤ በቤተክርስቲያንና በሃገር ላይ የታሰበ የታቀደ የጠላት ስራ እንዲፈርስ
ርኩሰትን የሚያስፋፋውን፤ግልሙትና፤ ግብረሰዶም
በቦታችን ላይ የተነሳውን ተግዳሮት በመቃወም እንጸልይ !
28 viewsedited 13:40