ቀን 6/11/2014 ዓ.ም
''የህዝብ አመኔታን መቼም ቢሆን አንዘነጋም፤ ክብራችን ህዝብን በፍትሃዊነት ማገልገል ነው'' ከንቲባ አዳነች አቤቤ
የህዝብ አመኔታን መቼም ቢሆን አንዘነጋም፤ ክብራችን ህዝብን በፍትሃዊነት ማገልገል ነው ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለፁ።
ከንቲባዋ በማህበራዊ የትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፦ ሌቦችና እምነታቸውን ሸጠው የሚበሉ ሁሉ ለጊዜው ቢታግሉንም አያሸንፉንም፤ ምንጊዜም እውነት ታሸንፋለች ብለዋል።
አክለውም ከሁሉም በላይ የህዝብን ሀብት በቴክኖሎጂ ዉንብድና ከመዘረፍ ማዳን ችለናል ነው ያሉት።
የጋራ መኖሪያ ቤቶች እጣ አወጣጥ ስራ ላይ አጠራጣሪ ጉዳዮች ከገጠሙ ጊዜ አንስቶ በማጣራት ሂደት ለደገፉ፤ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር፣ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ፣ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴርንና የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ከንቲባዋ ምስጋና አቅርበዋል።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!
You Tube:
Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau
Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc
Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication
Blog: - http://www.aacaebc.wordpress.com/
Website: - aaceb.gov.et
Email;- aacaebc@gmail.com
Instagram: - https://www.instagram.com/aacaeb/
ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!