Get Mystery Box with random crypto!

Wolaita Soddo Christan students fellowship(wscsf)Gf

የቴሌግራም ቻናል አርማ wscsfgf — Wolaita Soddo Christan students fellowship(wscsf)Gf W
የቴሌግራም ቻናል አርማ wscsfgf — Wolaita Soddo Christan students fellowship(wscsf)Gf
የሰርጥ አድራሻ: @wscsfgf
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 361

Ratings & Reviews

1.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2023-03-24 17:32:27

137 views14:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-14 12:42:21 እንጀራ ልንበላ አልተከተልንህም
ሃብት ብልጥግና ወደ አንተ አልጠራንም
ለምድር በረከት ታይቶ ለሚጠፋ
መች ደምህ ፈሰሰ ለሚያልፍ ተስፋ

የዘላለም ሕይወት ማግኘታችን ጉዳይ
ሁሌም ብርቃችን ነው ከምን ጋር ሊተያይ
ሕይወት ያካፈልከን ኢየሱስ አንተ ነህ
ሌላ አላየንም በነፍሱ የጨከነ

ግን ዛሬ ሲመጣ በየአደባባዩ
ትኩረት የሚፈልግ የሚል እኔን እዩ
አንተን አደብዝዞ ራሱን የሚያጐላ
አባብሎ ወሰደን ሆነናል ተላላ

አቤቱ ሕዝብህን መልሰን
ሳንጠፋ ቀድመህ ድረስልን
አቤቱ ልጆችህን አስበን
ከድፍረት ከውድቀት ታደገን

በጐ በሚመስል ሃሳብ እየተሳበ
በመልካም ንግግር ሕዝብ ተሰበሰበ
ዓመጸ ማይከለክል የረሳ ፍርድህን
እራሳችንን እንዳናይ አደንዝዞ አሰረን
በዘመን ፍጻሜ ጫፍ ላይ ቆመን ሳለን
ልባችን እንዳያይ ምንው ተደለለ

ዘይታችንን እንሙላ ጊዜው ሳይገባደድ
ፈጥነን እንመለስ ከሄድንበት መንገድ
አቤቱ ሕዝብህን መልሰን
ሳንጠፋ ቀድመህ ድረስልን
አቤቱ ልጆችህን አስበን
ከድፍረት ከውድቀት ታደገን
- መስከረም ጌቱ -
60 views09:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-13 16:58:59 ከጥቂት ዓመታት በፊት በሱዳን የሚኖሩ የአግልግሎት አጋሮቻችን እርዳታን ጠየቁን።በምሥራቅ ሱዳን የኢትዮጵያና የኤርትራ ድንበር አጠገብ የምትገኝ አሮማ የምትባል ከተማ በጋሽ ወንዝ ሙላት ምክንያት በጎርፍ ተጠለቅልቃ ነበር።ጎርፉም 7000 ያህል ቤቶችን አውድሞ ነበር።አጋሮቻችንም ገንዘብ አሰባስበን ብንረዳቸው ለአሮማ ሕዝቦች እንደሚያደርሱላቸውና ይህም መልካም ሥራቸው ለወንጌል በርን እንደሚከፍተላቸው ነገሩን።እኛም ይህንን ዜና በገንዘብ ለሚደግፉን አሜሪካውያን አጋሮቻችን አካፈልናቸው።ሁለት ወጣት እጮኛሞች ከተጠየቀው ገንዘብ አብዛኛውን ሰጡንና ለአሮማ ሕዝቦች በችግራቸው ልንደርስላቸው ቻልን።ከጥቂት ጊዜ በኋላ የእነዚህን ለጋስ ጥንዶች ታሪክ ሰማሁና ለእግዚአብሔር ያላቸውን ፍቅር መረዳት ቻልኩ።

እነዚህ ሰርገኞች በሱዳን ስለደረሰው የጎርፍ አደጋ የሰጠነውን መግለጫ ሲሰሙ ሊሞሸሩበት ያቀዱትን ድል ያለ ድግስ ቅልብጭ ባለችው ለወጡት።በሆቴል ቤት የመጋባት አሳባቸውንም ቀይረው በአንድ ግለሰብ ጓሮ ቤት አደረጉት።ብሎም ታዳሚ እንግዶቻቸው ለሰርጉ የሚሆነውን ምግብ በየቤታቸው አዘጋጅተው ይዘው እንዲመጡ አደረጉ።ለትልቅ ሰርግ ያሰቡትን ገንዘብ ወደ ሱዳን እንድንልከው ሰጡን።በዚህም ለብዙ የጎርፍ አደጋ ተጠቂዎች በረከት ሆኑ።

እግዚአብሔርን መውደዳችን ሙሉ የሚሆነው እንደዚህ ባልንጀራችንን ስንወድ ነው።...


ማርቆስ ዘመደብርሃን(ዶ/ር) ፤ልኡካን፤ገጽ 26-27

ከመጽሐፍት ማዕድ
66 views13:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-06 20:59:18 DAILY BREAD
ይቅርታ

         ማርቆስ 11፥20-26

ዓላማ-  አባታችን እግዚአብሔር ወደ ፊቱ በፀሎት ቀርበን የምንለውን ቃላችንን ብቻ ሳይሆን የምናድርገውን የዕለት ተዕለት የህይወት ምልልሳችንንም ያያል ያውቃልም። ይቅርታውን ፈልገን ወደ እርሱ ስንመጣ ሌላውን ይቅርታችንን ነፍገን ከሆነ እርሱም እንደ ቃሉ ይቅርታውን ይከለክለናል።

ቁልፍ ጥቅስ - “ለጸሎትም በቆማችሁ ጊዜ፥ በሰማያት ያለው አባታችሁ ደግሞ ኃጢአታችሁን ይቅር እንዲላችሁ፥ በማንም ላይ አንዳች ቢኖርባችሁ ይቅር በሉት።”
  — ማርቆስ 11፥25

የፀሎት ርዕስ - እስቲ ወደ ህይወታችን እንመልከት። ይቅር ያላልናቸው ምንያህል ሰዎች አሉ? ስለዚህ እግዚአብሔር ያሳየንን ምህረትና ይቅርታ እኛም ለሌሎች እንድናሳይ ጸጋው እንዲረዳን እንፀልይ።

TRUE LOVE
ONE FAMILY
STRONG FELLOWSHIP

የማርቆስ ወንጌል ጥናት

#ታማኝ_የመንግስቱ_ምስክሮች
#Faithful_Witnesses_of_the_Kingdom
#DigitalEvangelismMedia
@WolaitaSodoEvaSUE
4 views17:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-04 19:19:09 ወደ ፊልጵስዩስ 2
14-15፤ በመጥፎና በጠማማ ትውልድ መካከል ያለ ነቀፋ የዋሆችም ነውርም የሌለባቸው የእግዚአብሔር ልጆች እንድትሆኑ ሳታንጐራጉሩ ክፉም ሳታስቡ ሁሉን አድርጉ፤
35 views16:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-04 10:22:24 12 በፈተና የሚጸና ሰው የተባረከ ነው፤ ከተፈተነ በኋላ ለሚወዱት ተስፋ ስለ እርሱ የሰጣቸውን የሕይወትን አክሊል ይቀበላልና።
37 views07:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-19 11:58:27 DAILY BREAD
ድንገትኛ አልነበረም!

         ማርቆስ 10፡32-34

ዓላማ- የክርስቶስ ሞት እና ትንሳኤ ዛሬ ብዙ ሰዋች እንደሚሉት አጋጣሚ ወይም ድንገተኛ ወይም እውነት ያልሆነ ተረት አየደለም። ይሄ ሁሉ ገና ሳይፈጥር ክርስቶስ ምን ሊሆን እንዳለ ያቅ ነበርና።

ቁልፍ ጥቅስ - " እንዲህም አላቸው፤ “ወደ ኢየሩሳሌም እንወጣለን፤ የሰው ልጅ ለካህናት አለቆችና ለጸሐፍት ዐልፎ ይሰጣል፤ እነርሱም የሞት ፍርድ ይፈርዱበታል፤ አሳልፈው ለአሕዛብ ይሰጡታል፤ ያፌዙበታል፤ ይተፉበታል፣ ይገርፉታል፣ ከዚያም ይገድሉታል፤ እርሱ ግን ከሦስት ቀን በኋላ ይነሣል።” — ማርቆስ 10:33-34

የፀሎት ርዕስ - እግዚአብሔር አቅዶና አስቦበት ሰለሰራው እኛን የማዳን ስራ እናመስግነው።

TRUE LOVE
ONE FAMILY
STRONG FELLOWSHIP

የማርቆስ ወንጌል ጥናት

#ታማኝ_የመንግስቱ_ምስክሮች
#Faithful_Witnesses_of_the_Kingdom
#DigitalEvangelismMedia
@WolaitaSodoEvaSUE
48 views08:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-17 17:07:17 የእግዚአብሔር መንግስት፡ የመንግስቱ ባህሪያት ክፍል 1 | ሮቤል ጨመዳ | መንግስትህ ትምጣ S1:E7


52 views14:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-16 18:36:54 DAILY BREAD
ይሻልሃል...

         ማርቆስ 9፥14-32

ዓላማ -  ክርስቶስ ስለ ኃጢአት ሲያስተምር  ምን ያህል አደገኛ እና ሰውን ወደ እሳት ባህር መጣል እንደሚችል ተናግሯል። እኛም ይህንን አውቀን ከኃጢአት ልንርቅ ይገባናል።

ቁልፍ ጥቅስ — “ዓይንህ ብታሰናክልህ አውጣት፤ ሁለት ዓይን ኖሮህ ትላቸው ወደማይሞትበት እሳቱም ወደማይጠፋበት ወደ ገሃነመ እሳት ከመጣል አንዲት ዓይን ኖራህ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት መግባት ይሻልሃል።” — ማርቆስ 9፥47-48

የፀሎት ርዕስ - በህይወት ዘመናችን ሁሉ ከኃጢአት ሊያነጻን ደግሞም በቅድስና ሊያኖረን ወደሚችለው ወደ እግዚአብሔር መቅረብ እና ከእርሱ ጋር መሆን እንዲሆንልን። በኃጢአት ላይ መጨከን የምንችልበትን ጸጋ እንዲሰጥን።

TRUE LOVE
ONE FAMILY
STRONG FELLOWSHIP

የማርቆስ ወንጌል ጥናት
#ታማኝ_የመንግስቱ_ምስክሮች
#Faithful_Witnesses_of_the_Kingdom
#DigitalEvangelismMedia
@WolaitaSodoEvaSUE
54 views15:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-13 23:24:58 Channel photo updated
20:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ