Get Mystery Box with random crypto!

#Remedial_Exam የሪሜዲያል ሀገር አቀፍ ማጠቃለያ ፈተና የሦስተኛ ቀን ውሎ በወላይታ | Wolaita Sodo University

#Remedial_Exam

የሪሜዲያል ሀገር አቀፍ ማጠቃለያ ፈተና የሦስተኛ ቀን ውሎ

በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ለሪሜዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች እየተሰጠ ያለው ሀገር አቀፍ ማጠቃለያ ፈተና ሦስተኛ ቀኑን ይዟል።

ዛሬ ሰኔ 28/2015 ዓ.ም ዕለተ ረቡዕ በሁለቱም የተፈጥሮ እና ማሕበራዊ ሳይንስ መስክ ተማሪዎቹ የኬሚስትሪ እና የጄኦግራፊ ፈተና ተፈትነዋል።
_________

በዩኒቨርሲቲው ሦስተኛ ቀኑን በያዘው የሪሜድያል ሀገር አቀፍ ማጠቃለያ ፈተና በሁለቱም የተፈጥሮ እና ማሕበራዊ ሳይንስ መስክ ተማሪዎች የኬሚስትሪ እና የጄኦግራፊ ፈተና ተፈትነዋል።

ዛሬ በተሰጠው የኬሚስትሪ እና የጄኦግራፊ ፈተና በአጠቃላይ 5 ሺሕ 625 ተማሪዎች የተፈተኑ ሲሆን፤ ከጠቅላላ ተፈታኝ ተማሪዎች 3 ሺሕ 282 የተፈጥሮ እና 2 ሺሕ 374 የማሕበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ናቸው።

የፈተናው ሂደት ፍጹም ሰላማዊ ሆኖ መጠናቀቁን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ታከለ ታደሰ ያሳወቁ ሲሆን፤ የፕሮግራሙ ማጠቃለያ ሀገር አቀፍ የፈተና ሂደት እስከ ሰኔ 30/2015 ዓ.ም ባሉት ተከታታይ ቀናት በዩኒቨርሲቲው የሚሰጥ መሆኑንም ተናግረዋል።

ፕሬዝዳንቱ አክለውም፤ ተፈታኝ ተማሪዎች የፈተናውን ህጎች በማክበር እና ሥነ-ምግባር ተላብሰው እንዲፈተኑ ያሳሰቡ ሲሆን፤ በቀጣይ አመት መደበኛ የዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን መቀጠል የሚያስችላቸውን ማለፊያ ውጤት እንዲያስመዘግቡ መልካም ምኞታቸውንም ገልጸዋል።

የፈተናው ሂደት ሰኔ 28/2015 ዓ.ም ዕለተ ሐሙስ ከቀኑ 9 ሰዓት ሲቀጥል ለሁለቱም የተፈጥሮ እና ማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች የእንግሊዘኛ ፈተና የሚሰጥ መሆኑ ተመላክቷል።

➭ «ዕውቀትን በተግባር!!»

የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት!!

➤ ሰኔ 28/2015 ዓ.ም

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት

ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/profile.php?id=100063820159424

ቴሌግራም፡ https://t.me/WolaitaSUniversity

ዩቲዩብ፡ https://www.youtube.com/channel/UC6VukdZbl5iVgZGXG8BkMdw/videos

ዌብሳይት፡ http://www.wsu.edu.et/

ትዊተር፡ https://twitter.com/WSodoUniversity?t=w_VzjrOWj3D3Mc8BKlQFXA&s=09

ሊንክዲን፡ https://www.linkedin.com/company/wolaita-sodo-university/

ኢንስታግራም፡ https://instagram.com/wolaita_sodo_university?igshid=YmMyMTA2M2Y=

አብራችሁን ስለሆናችሁ እናመሰግናለን