Get Mystery Box with random crypto!

ውሉደ ብርሃን ሚድያ

የቴሌግራም ቻናል አርማ weludebirhan — ውሉደ ብርሃን ሚድያ
የቴሌግራም ቻናል አርማ weludebirhan — ውሉደ ብርሃን ሚድያ
የሰርጥ አድራሻ: @weludebirhan
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ሀገር: ኢትዮጵያ
ተመዝጋቢዎች: 2.35K
የሰርጥ መግለጫ

የመካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤ/ክ ውሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት መንፈሳዊ ጽሑፎችን፣ ወቅታዊ ሁኔታዎችን የሚገልፁ መረጃዎችን እንዲሁም ማስታወቂያዎችን የምንለቅ ስለሆነ እንድትከታተሉን እንጠይቃለን።
👋👋👋👋👋👋👋👋👋👋
መልእክት ካሎት በዚህ ሊንክ ይላኩልን
⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️
@saint_kirkos

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-07-31 14:58:30
እሁድ ሐምሌ 24/2014 ዓ.ም

በደብራችን በመካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ለረዥም ዓመታት ከ1966 ዓ.ም.ጀምሮ በልዩ ልዩ መንፈሳዊ የአገልግሎት ዘርፍ ያገለገሉ አንጋፋ ካህናት አባቶች ላበረከቱት መልካም አስተዋጾ"ዝክረ አበው" በሚል መሪ ቃል በደብራችን አስተዳዳሪ መላከ ፀሐይ ቆሞስ አባ ኪዳነ ማርያም ዮሴፍ የዕውቅና የሽልማት መርሐ ግብር ተከናወነ ።
የዕውቅናው መርሐ ግብር ሀሳብ አመንጪ እና አስተባባሪ መልአከ ሰላም ቀሲስ ወንደሰን በቀለ መሆናቸውን በመርሐ ግብሩ ላይ ተገጿል።
862 viewsBisrat, 11:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-29 15:17:21
የሰንበት ት/ቤታችን አባላት የሆኑት አቶ ተገኝወርቅ ተሾመ (ኩኩሻ) ከነ ባለቤታቸው ለጥምቀተ ባህር ፕሮጀክት 30‚000ብር በማውጣት 24 ቤርጋ ብረት ገዝተው ገቢ አድርገዋል፡፡
እንዲሁም ጸዲ ምግብ ቤት (ዳዊት) አንድ ሲኖ አሸዋ ገቢ አድርገዋል፡፡ እግዚአብሔር አምላካችን ወንድሞቻችንና እህቶቻችንን በጤንነትና በሀብት አብዝቶ ይባርካቸው እያልን ሌሎቻችንም ከበረከቱ እንድንሳተፍ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡
890 viewsBiruk, 12:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-29 11:34:07 ነገ እኮ ሐምሌ 22 #ቅዱስ_ዑራኤል
በነጎድጓድና በመባርቅት ላይ ለተሾመ ለመልአኩ ለቅዱስ #ዑራኤል አመታዊ ክብረ በአል እንኳን አደረሰን
በመላእክት ከተማ በራማ ካሉት ሦስት ነገዶች ዉስጥ አንዱ ነገድ ሥልጣናት ይባላል፡፡ በሥልጣናት ላይ ከተሾሙ ሊቃነ መላእክት ዉስጥ አንዱ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሱርያል ይባላል፡፡ሱርያል የሚለዉ ስም በአንዳንድ ድርሳናት ካልሆነ በስተቀር እምብዛም አይታወቅም ትርጉሙም ‹‹‹ዐለቴ እግዚአብሔር ነዉ››› ማለት ነዉ፡፡ ሱርያል የቅዱስ ዑራኤል ሌላ ስሙ ነዉ፡፡ ዑራኤል ማለት ‹‹‹እግዚአብሔር ብርሃን ነዉ›››ማለት ነዉ፡፡ በቤተ ክርስቲያንም በስፋት የሚተወቀዉ ስም ዑራኤል የሚለዉ ስም ነዉ፡፡/ድርሳነ ዑራኤል 1991 ገጽ 14/ በመጽሀፍ ቅዱስ ዉስጥ ስለ ቅዱስ ዑራኤል በስፋት የምናገኘዉ በመጽሐፈ ዕዝራ ሱቱኤል ነዉ፡፡
ዕዝራን ይራዳዉ የነበረ ፤ለዕዝራም ጠፍተው የነበሩ የብሉይ ኪዳን መጻህፍትን እንደ ገና እንዲጽፋቸዉ ጽዋ ልቦና አጠጥቶ ምሥጢር የገለጠ ቅዱስ ዑራኤል ነዉ፡፡(ዕዝ ሱቱ2 )፡፡
‹‹‹በመብረቅና በነጎድጓድም ላይ የተሾመ ታላቅ መላክ ነዉ››››ሄኖክ 6፡2
ምሥጢረ ሰማይም ለሄኖክ ያሳየዉ ዕዉቀትን የገለጠለት እርሱ ቅዱስ ዑራኤል መሆኑን ጽፏል፡፡(ሄኖክ 28፡13-14)፡፡
እመቤታችንም በኪደተ እግርዋ ኢትዮጵያን በዞረች ጊዜ ቅዱስ ዑራኤል ያገለግላት እንደነበርና እንዳስጎበኛትም በድርሳነ ዑራኤል ተጽፏል ፡፡
ለአዳም የድህነትን ዜና የነገረዉ ቅዱስ ዑራኤል ነዉ ዮሴፍን ብርታት ሰጥቶ ከብእሲት ጲጥፋራ ያዳነዉ ቅዱስ ዑራኤል ነዉ ለእዝራ ምሥጢር የገለጠለት ቅዱስ ዑራኤል ነዉ የሚያረጋጋ ለኃጢያተኞች ምህረት የሚለምን መልአክ ነዉ፡፡(ስንክሳር ጥር)
ለአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫም በሐይቅ እስጢፋኖስ ለገዳሙ መነኮሳት እህል እየፈጨ ዉሃ እየቀዳ እመቤታችንን እየተማጸነ ሲኖር አንድ ቀን ከሥዕሏ ሥር እየሰገደ ሳለ መልአኩ ዑራኤል ተገልጦ ጽዋህ ልቦና አጠጣዉ፡፡ከዚያ ጀምሮ ምሥጢረ ሰማይ ወምድር ተገልጦለት ከ 40 በላይ መጻህፍትን ደርሷል፡፡ (መጽሐፈ አርጋኖን )
በእለተ ስቅለት የጌታ ደሙን በብርሃን ፅዋ ተቀብሎ በዓለም የረጨ ቅዱስ ዑራኤል ነው
ሐምሌ 21 እና 22 ቅዳሴ ቤቱ የሚከበርበትእና እዝራ ሱቱኤልን የእውቀት ጽዋ ያጠጣበት ነው በአምላኩ አማላጅነቱን ኑና ተማጸኑት። በጸሎቱ ለተማጸነ ከአምላኩ በረከትን ምህረትን የሚያሰጥ አዛኝ እርሩህ መልአክ ነው። አሁንም ይህ ዓለም በአማላጅነቱ አምኖ ጸበሉን ቢጠጣ ከክፉ በሽታ እንደሚፈወሱ ቃለ ኪዳን ተሰጥቶታል፣በፍጹም መጠበቅን ጠብቆ ለዚህ ያደረሰን አምላካችን ክብርና ምስጋን አምልኮትና ውዳሴ ይድረሰውና ይህን ታላቅ መልዕክ በችሎታችን መጠን እንድናመሰግን ና እንድናገለግል እግዚአብሔር ይርዳን አምላክ ባለንበት ከሁላችን ጋር ይሁን ከመልዐኩ ከቅዱስ ዑራኤል በረከት ረድኤት ያሳትፈን፡፡
ለእዝራ ለአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ዕዉቀትን የገለጸ መልአክ ለኛም ይለመነን "አሜን"

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
849 viewsBiruk, 08:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-29 11:30:44
728 viewsBiruk, 08:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-29 08:27:20
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ሐምሌ ሃያ ሁለት በዚህች ቀን ሰማዕተ ጽድቅ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ቤተክርስቲያን በአደራነት የሰጠቻቸውን ኃላፊነት ለመወጣት ሕዝበ ክርስቲያኑን በጸሎታቸው እየደገፉ በትምህርታቸው እያበረቱ በማስተዳደር ላይ እንዳሉ በ1928 ዓ.ም በአረመኔው የኢጣልያ ፋሺስት በግፍ የተገደሉበትና ሰማዕትነት የተቀበሉበት ዕለት ነው።
በረከታቸው ከሁላችን ጋር ይሁን
770 viewsBiruk, 05:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-29 08:27:01
726 viewsBiruk, 05:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-27 16:32:55

988 viewsBiruk, 13:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-27 10:57:39
831 viewsSolu Aklil, 07:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-26 21:49:46

862 viewsBiruk, 18:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ