በመጪው ሐምሌ ከሚሰጠው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና አስቀድሞ፤ ሞዴል የ12ኛ ክፍል ፈተና በሰኔ መጨረሻ በአማራ ክልል እንደሚሰጥ የክልሉ ትምህርት ቢሮ አሳውቋል። ሞዴል ፈተናው ተማሪዎቹ የሚያደርጉትን ዝግጅት እንደሚያግዝ የቢሮው ኃላፊ ማተብ ታፈረ (ዶ/ር) ለአሚኮ ተናግረዋል። በክልሉ 215,590 ተማሪዎች የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ለመውሰድ መመዝገባቸው ይታወቃል። በባለፈው ፈተና የታዩ የሥነ ምግባር ችግሮች በዚህ ዓመት እንዳይደገሙ ተከታታይ የሆኑ ሥራዎች እየተሠሩ እንደሚገኙ ኃላፊው ገልጸዋል። Share us https://t.me/Temhert_Minister 935 views𝐖𝐞𝐥𝐥 𝐨𝐰𝐧𝐞𝐫, 20:14