Get Mystery Box with random crypto!

የአላማጣ እምቢተኝነትና የህወሓት ጭንቀት የአላማጥን ነዋሪዎች በብረት መዳፌ ቀጥቅጬ ካልገዛሁ የሚለ | 🗣 ወቅታዊ_መረጃ 🇪🇹

የአላማጣ እምቢተኝነትና የህወሓት ጭንቀት
የአላማጥን ነዋሪዎች በብረት መዳፌ ቀጥቅጬ ካልገዛሁ የሚለው አሸባሪው ህወሓት ከፍተኛ ሕዝባዊ እምቢተኝነትና ተቃውሞ እየገጠመው ይገኛል፡፡
ሰሞኑን አላማጣ አካባቢ ስብሰባ የጠራው አሸባሪው ህወሓት በሰዎች አጀብ ይጨናነቃል ያለው መድረክ በጣት የሚቆጠሩ ሰዎች ያውም የቡድኑ ደጋፊዎችና አባላት ብቻ የተገኙበት መሆኑ አስደንግጦታል፡፡ ይህ ሕዝባዊ እምቢተኝነት አንዳች የተደበቀ ነገር ከጀርባው አዝሏል በሚልም ጭንቀት ውስጥ ገብቷል፡፡
እንደ አሸባሪ ቡድኑ ግምገማ ትናንት እንደ ልቡ የሚያዘው ኅብረተሰብ ዛሬ የልብ ልብ ተሰምቶት ፊቱን ያዞረበት በጀግናው የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የሚመራው ጥምር ጦር ወደ ቀጣናው መግባቱ አይቀርም በሚል ነው፡፡  
በዚህ ስሌት የተደነባበሩት በአላማጣ አካባቢ የሚንቀሳቀሱ  የህወሓት አመራሮች እና መረጃ አቀባዮች ሁኔታው ተባብሶ ከቀጠለ ሕዝቡ  ከእምቢተኝነት አልፎ  ግልጽ ወደ ሆነ ተቃውሞ ይሸጋገራል የሚል ሥጋት ውስጥ ወድቀዋል፡፡ ነገም ኅብረተሰቡ ለጥምር ጦሩ አሳልፎ ይሰጠናል በሚል ከአካባቢው ለመሸሽ ቢያስቡም፤ አሸባሪው ህወሓት ከወረዳ ወደ ወረደ የመንቀሳቀስ እገዳ በመጣሉ ከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ መግባታቻው ታውቋል፡፡

ሼር በማድረግ ትክክለኛዉን መረጃ ለሌሎች ተደራሽ ያድርጉ። ለበለጠ መረጃ ቴሌግራም
@wektawi_Merej