Get Mystery Box with random crypto!

ግተህ የተቀመጥህ አንተ ነህ። የአብን ፈቃድ ትፈጽም ዘንድ ከሰማየ ሰማያት ወደዚህ ዓለም የመጣህ አ | ውዳሴ ማርያም/wdasemaryam

ግተህ የተቀመጥህ አንተ ነህ። የአብን ፈቃድ ትፈጽም ዘንድ ከሰማየ ሰማያት ወደዚህ ዓለም የመጣህ አንተ ነህና ክቡር ምስጉን አምላክ ነህ።
ለአማዑቲከ
መድኃኔ ዓለም ሆይ፤
የኃጥኡን ሰው ውሳጣዊና አፍአዊ ሰውነቱን ለሚቀድሰው ንዑድ ክቡር ለሚሆን ውስጣዊ ገንዘብህና ለአማዑትህም ሰላም እላለሁ።
ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ፤
ከዚህ ዓለም ጥፋትና ጥል ፡ ጭቅጭቅና ንዝንዝ ሁሉ አድነኝ። በሰማይና በምድር፤ በባሕርና በየብስም ቢሆንም ያለአንተ ቸር ሰው ወዳጅ ንጉሥ የለምና።
ለሕንብርትከ
መድኃኔ ዓለም ሆይ፤
በአምሳለ ቅዱስ መስቀል ማዕተብነ፤ በግብረ መንፈስ ቅዱስ ለተማተበው ሕንብርትህ ሰላም እላለሁ።
ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ፤
አቤቱ ከችግርና ከፈተና አድነኝ፤ አባትህም በምስሐ ደብረጽዮን በሚያደርገው ታላቅ የምሳ ግብዣ ላይ ይዘኸኝ ግባ ከአንተ በቀር ሌላ የማውቀው ዘመድ የለኝምና።
ለሐቌከ
መድኃኔ ዓለም ሆይ፤
የሲኦልን በር የናሱን መዝጊያ ቀጥቅጠህና ሰባብረህ የብረቱንም ቁልፍ እንደ ሰም አቅልጠህ ነፍሳትን ከሲኦል በአወጣህበት ሰዓት መለኮታዊ ዝናርን ለታጠቀ ወገብህንና ኃይለአርያምን ለተጎናጸፉ አቍያጾችህም ሰላም እላለሁ።
ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ፤
መሐሪ ይቅር ባይ አንተ እግዚአብሔር እንደመሆንህ መጠን በምሄድበት መንገድ ሁሉ ቀናውን ጎዳና ምራኝ። የጽድቁንና ዕውነተኛውን መንገድ ፈጽሞ ለማወቅ አልችልምና።
ለአብራኪከ
መድኃኔ ዓለም ሆይ፤
ከሁለቱ እግሮችህ ጋር ወደ ብሔረ ሞት በፈለሱ ጊዜ በደም ቅንዋት ለተጥለቀለቁ ጉልበቶችህ ሰላም እላለሁ።
ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ፤
ቃልህ የማይታበይ ዕውነተኛ አምላክ ነህ፤ አቤቱ ጌታዬ እኔን አገልጋይህን ለመጎብኘት በየጊዜው በመመላለስ ወደ እኔ ና ና አቤቱ ጌታዬ አንተ የዓለም ግርማ ሞገሱ ነህና።
ለሰኰናከ
መድኃኔ ዓለም ሆይ፤
ፈጻሜ ፍቅር ወሰላም ለሆነው ተረከዝህ ሰላም እላለሁ። ዓለሙን ለማዳን ከሰማየ ሰማያት የወረድህ አንተ ቸር አምላክ ነህ፡
ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ፤
የአርያም ጽንዕ ኃይል ስትሆን እንደደካማ ሰው ክቡዱንና ግዙፉን ዕፀ መስቀል በመሸከም ምንኛ ድካምንና መከራን ልትታገስ ቻልክ። ለዚህ ረቂቅ ትሕትናህ አንክሮ ይገባል።
ለመከየድከ
መድኃኔ ዓለም ሆይ፤
ያለበደልና ያለአበሳ ሰውና መላእክትን የፈጠርክ ሆይ በብረት ችንካር ለተቸነከሩት ጫማዎችህ ሰላም እላለሁ
ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ፤
አቤቱ ጌታ መሐሪ ይቅር ባይና ቸር እግዚአብሔር እንደመሆንህ መጠን በዚያ የቁርጥ የፍርድ ቀን በምትመጣበት ጊዜ ማረኝ ይቅርም በለኝ አቤቱ በፊትህ እንደ እኔ ያለ በደለኛ የለምና
ለአጸብዓከ
መድኃኔ ዓለም ሆይ፤
በለቢሰ ስጋ ለደከሙና ለወዙ ጣቶችህ ሰላም እላለሁ። በጎዳና ላይ በድንጋይ ዕንቅፋት ላልተሰናከሉ ለእግሮችህ አጽፋርም ሰላም እላለሁ።
ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ፤
ፍለጋህ ተመራምሮ ሊገኝ የማይቻል ነው። አቤቱ የወዳጅህ የዳዊት መጽሐፍ እንደተናገረው በዚህ ዓለም ስለዕውነት ስለጽድቅህ የደከመ በወዲያኛው ዓለም የዘላለም ሕይወት እንዳለው አምናለሁ ተስፋም አደርጋለሁ።
ለቆምከ
መድኃኔ ዓለም ሆይ፤
አይሁዶች ተሰባስበው በቀራንዮ አደባባይ ለአቆሙት አካለ ቆምህ ሰላም እላለሁ።
ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ፤
ግዙፍ ሥጋን በተላበሰ አንደበቴ ልመናዬን ሳቀርብልህ አሳልፈህ ለጠላት አትስጠኝ።እንዳንተ ያለ ጠቃሚ ዘመድ በቂ ወገን አይገኝምና።
ለመልክእከ
መድኃኔ ዓለም ሆይ፤
ለጻድቃን ያይደለ ኀጥአንን ለማዳን በራሱ ደም ራሱ ለተጥለቀለቀ ሥነ መልክእህ ሰላም እላለሁ።
ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ፤
በየጊዜው በነጋ በጠባ ወደ አንተ እገሠግሣለሁ። በመስቀል ላይ ሳለህ አባት ሆይ፤ ይቅር በላቸው በማለት የተናገርከውን የቸርነትና የርኀራኄ ቃል አስቀድሜ ሰምቻለሁና።
ለፀአተ ነፍስከ
መድኃኔ ዓለም ሆይ፤
በመስቀል ላይ ልዩ ልዩ አምላካዊ ተአምራትንና ሕማማተ መስቀል ከተፈጸመ ቡኃላ በገዛ ሥልጣንህ ለተፈጸመው ጸዓተ ነፍስህ ሰላም እላለሁ።
ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ፤
ዓለምን ለማዳን በተሰቀልክበት በዚያን ሰዓት እንሆ ጌታዬ ሆይ፤ ፀሐይ ብርሃኑን ከመስጠት ተከልክሎ ጊዜው ጨለመ ጨረቃም ደም ሆነ።
ለግንዘተ ሥጋከ
መድኃኔ ዓለም ሆይ፤
ከጽጌረዳ መዓዛ ይልቅ መዓዛ ላለው ግንዘተ ሥጋህ ሰላም እላለሁ። በኢየሩሳሌም አደባባይ ለሚገኘው መካነ መቃብርህ ሰላም እላለሁ።
ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ፤
ሰይጣናዊ በሆነ በይሁዳ ወገኖች ቅናት ሞተህ የሔዋን ልጆች ባልተቀበሩበት አዲስ የሚሆን በታነፀ የሕንጻ መቃብር ተቀበርህ። አቤቱ ሞት የማይገባህ ላንተ ምስጋና ይገባል።
ለትንሣኤከ
መድኃኔ ዓለም ሆይ፤
የመቃብር ጠባቂ ጭፍሮችን አሸብሮ የጻድቃንን ትንሣኤ ለገለጠው ትንሣኤህ ሰላም እላለሁ።
ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ፤
በልዩ ትንሣኤህ ጨለማን ካስወገድህ ቡኃላ በግብር አምላካዊ በዝግ ቤት ገብተህ ደቀመዛሙርትህን በጦር የተወጋውን ጎኔን በችንካር የተቸነከሩ እጅ እግሬን ተመልከቱ አልካቸው።
ለትንሣኤከ
መድኃኔ ዓለም ሆይ፤
ከእንቅልፍ እንደመንቃት ለሆነ ትንሣኤህ ሰላም እያልኩ ስፍር ቁጥር የሌላቸውን ተአምራትህን እናገራለሁኝ።
ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ፤
ለአዳም ልጆች መድኀን እንደመሆንህ መጠን የእኔን የደካማውን አገልጋይህን ልመና ተቀብለህ አቤቱ ከዚያ ርጉም ከሚሆን ጠላቴ እጅ አድነኝ።
ለዕርገትከ
መድኃኔ ዓለም ሆይ፤
በዓውሎ ንፋስ በእሳተ ነበልባል አምሳል መንፈስ ቅዱስን ትልክልን ዘንድ በነጎድጓድና በመባርቅት የሠረገላ ዘባን ለተከናወነ ዕርገትህ ሰላም እላለሁ።
ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ፤
በአንዲት መንግሥትህ መንግሥቱን ለዘላለም አገዛዙም ለትውልደ ትውልድ ነው እያሉ ሰማያውያን መላእክት በየዕለቱ በየሰዓቱ ያመሰግኑሃል።
ለዕርገትከ
መድኃኔ ዓለም ሆይ፤
የቃል ኪዳኑን ሥነ ሥረዓት ለፈጸመ ዕርገትህና ሁሉን ለማዘጋጀት በኃለኛው ዘመን አመጣጥህ ሰላም እላለሁ።
ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ፤
ቅድመ ዓለም በጌትነቱ ክብር ከአባትህ ዘንድ የነበረ ወደዚህ ዓለም በዓውሎ ነፋስ አምሳል የላክኸው እሱ መንፈስ ቅዱስ የኃጢአቴን እሾህ በማቃጠል አቤቱ እሱ ኃይሉን ይግለጽ።
አልቦ እምሰብእ
መድኃኔ ዓለም ሆይ፤
ከሰው ወገን ማንም እንደ እኔ ኃጢአት የሰራ በደለኛ የለም። እንደ አንተም ያለ መሐሪ ይቅር ባይ አምላክ አይኖርም።
ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ፤
ዓለማትን ሁሉ የፈጠርህ ፈጣሪ እንደመሆንህ መጠን በኃለኛው ዘመን በዓለም ላይ ለመፍረድ በምትመጣበት ጊዜ ከጎንህ በፈሰሰው ደም ኃጢአቴን እጠብልኝ አሜን።
አቄርበ ወትረ
መድኃኔ ዓለም ሆይ፤
ስለኃጢአቴ ሥርየት በጭንቅና በመከራምስጋናን ዘወትር አቀርባለሁ።
ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ፤
የሰማይና የምድር ጌታ እንደመሆንህ እኔ ጎስቋላው አገልጋይህን ኃጢአቴን ይቅር ብለህ ማደሪያዬን ስጠኝ እያልኩ በምለምንህ ጊዜ በዱርም ቢሆን በተራራ ላይ በአስፈላጊው ቦታ ሁሉ በፍላጎት መጠን ምግቤን አዘጋጅልኝ።
አጽምዓኒ
መድኃኔ ዓለም ሆይ፤
መሪር የሆነ የሰቆቃው ነገር የምጽፍልህ ነኝና በጆሮህ አድምጠኝ ቅዱሳን በሆኑ እጆችህ ጹሑፌን ተቀበለኝ።
ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ፤
መላእክት ሊቃነ መላእክት በመንቀጥቀጥ በፊትህ የሚቆሙ አንተ በጲላጦስ አደባባይ ቆምክ አቤቱ። ዬ ዬ ዬ ስለኛ እንደዚህ ዓለም ሰው ተቆጠርክ አቤቱ። ዬ ዬ ዬ አንተ አምላክ ስትሆን ስለኛ ጎንህን በጦር ተወጋህ አቤቱ! ።
ኦ ሊቀ ካህናት
መድኃኔ ዓለም ሆይ፤
አቤቱ የካህናት አለቃ ስትሆን እንደ ቀማኛ እንደዐመፀኛ እንደወንጀለኛ የራሄልና የልያ ልጆች የኃሊት አሰሩት።አቤቱ!።
ፈጣሪየ ክርስቶስ ሆይ፤
ስለኛ ለሞት ተላልፈህ ተሰጠህ አቤቱ።
ዬ ዬ ዬ ስለኛ በጦር ወጉህ። አቤቱ ዬ ዬ ንጹህ ክቡር ስጋህን መሬት ሸፈነው አቤቱ! ! ።
ኦ ክርስቶ