2021-10-01 17:19:47
#የሥላሴ_አስተምህሮ
#The_Doctrine_of_Trinity
==============================
#ክፍል_አራት (4)
#ሥላሴ_በብሉይ_ኪዳን
=================================
የሥላሴ አስተምህሮ በብሉይ የማይታወቅ በአዲስ ኪዳን የመጣ የሚመስላቸው ብዙዎች ናቸው። በብሉይ ኪዳን ያልነበረ እግዚአብሔር በአዲስ ኪዳን እንዴት ሊገለጥ ይችላል?
በአዲሱ ኪዳን የተገለጠው እግዚአብሔር በብሉይ ኪዳን የነበረው ከሆነ እንኪያስ የሥላሴ አስተምህሮ የሚጀምረው በአዲስ ኪዳን ሳይሆን በብሉይ ኪዳን መሆን አለበት።
መጽሐፍ ቅዱስን በስርዓት ስናጠና ከዘፍጥረት እስከ ራዕይ በብሉይም ሆነ በአዲስ ኪዳን የተፃፉ እውነታዎችን ስንመረምር መሸሽ በማንችል ሁኔታ ሶስት አካላት ያሉት አንድ አምላክ (ሥላሴ) እንዳለ ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻ ተፅፎ እናገኛለን ።
ቅዱሳን ሊያስተውሉት የሚገባ ነገር፦
================================
እግዚአብሔር አብ እግዚአብሔር ወልድ አይደለም እግዚአብሔር ወልድ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ አይደለም ሶስቱም የተለያዩ አካላት ናቸው ደግሞም አንድ አምላክ ነው።
ዘዳግም 6 (Deuteronomy)
4፤ እስራኤል ሆይ፥ ስማ፤ አምላካችን እግዚአብሔር አንድ እግዚአብሔር ነው፤
መፅሐፍ ቅዱስ ምን ይላል!!!
ሥላሴ በብሉይ ኪዳን
===================
#በብሉይ ኪዳን የሚገኙ በርካታ ጥቅሶችን ስንመለከት ሶስት የተለያዩ አካላት ያሉት አንድ አምላክ እንዳለ በግልፅ ይናገራሉ።
በዘፍጥረት መፅሐፍ እግዚአብሔር የሚለው ኤሎሂም (Elohim )የሚል የዕብራይስጥ ቃል ይጠቀማል።
ኤል== ኃያል አምላክ (ነጠላ ቁጥር) ሲሆን
ኤሎሂም== ኃያላን አምላኮች ( ብዙ ቁጥር) ይጠቀማል።
1) ዘፍጥረት 1፡1 በመጀመሪያ እግዚአብሔር (ኤሎሂም) ሰማይንና ምድርን #ፈጠረ።
እግዚአብሔር (ኤሎሂም) = ብዙ ቁጥር
ፈጠረ = ነጠላ ቁጥር
2) ዘፍጥረት 1፡26 እግዚአብሔርም( ኤሎሂም) #አለ፡— ሰውን #በመልካችን እንደ #ምሳሌአችን #እንፍጠር፤ የባሕር ዓሦችንና የሰማይ ወፎችን፥ እንስሳትንና ምድርን ሁሉ፥ በምድር ላይ የሚንቀሳቀሱትንም ሁሉ ይግዙ።
አለ= ነጠላ ቁጥር
በመልካችን,ምሳሌአችን,እንፍጠር = ብዙ ቁጥር
3) ዘፍጥረት 3፡22 እግዚአብሔር አምላክም #አለ፡— እነሆ አዳም መልካምንና ክፉን ለማወቅ #ከእኛ እንደ አንዱ ሆነ..
አለ= ነጠላ ቁጥር
ከእኛ እንደ አንዱ = ብዙ ቁጥር
4) ዘፍጥረት 11፡6-7 እግዚአብሔርም #አለ፡— ......
#ኑ፥ #እንውረድ፤ አንዱ የአንዱን ነገር እንዳይሰማው ቋንቋቸውን በዚያ እንደባልቀው።
አለ = ነጠላ ቁጥር
ኑ ፣ እንውረድ = ብዙ ቁጥር
5) ኢሳይያስ 6፡8 የጌታንም ድምፅ፡— ማንን #እልካለሁ? ማንስ #ይሄድልናል? ሲል ሰማሁ።
እልካለሁ? = ነጠላ ቁጥር
ይሄድልናል?= ብዙ ቁጥር
6) ኢሳይያስ 48 ፡15 -16፤ እኔ ራሴ ተናግሬአለሁ፤ እኔ ጠርቼዋለሁ፤ አምጥቼዋለሁ፥ መንገዱም ትከናወንለታለች።
፤ ወደ እኔ ቅረቡ ይህንም ስሙ፤ እኔ ከጥንት ጀምሬ በስውር አልተናገርሁም፤ ከሆነበት ዘመን ጀምሮ እኔ በዚያ ነበርሁ፥ አሁንም #ጌታ እግዚአብሔርና #መንፈሱ_ልከውኛል። ( ዩሐ ወንጌል 8:23-25)
ጌታ እግዚአብሔር = አብ
መንፈሱ= መንፈስ ቅዱስ=
ልከውኛል መሲሁ (ወልድ)
7) ኢሳይያስ 61 (Isaiah)
1፤ #የጌታ የእግዚአብሔር #መንፈስ #በእኔ ላይ ነው፥ ለድሆች የምሥራችን እሰብክ ዘንድ እግዚአብሔር ቀብቶኛልና፤ ልባቸው የተሰበረውን እጠግን ዘንድ፥ ለተማረኩትም ነጻነትን ለታሰሩትም መፈታትን እናገር ዘንድ ልኮኛል።
የጌታ እግዚአብሔር = አባት
መንፈስ = መንፈስ ቅዱስ
በእኔ ላይ ነው= መሲሁ (ወልድ)
8)መዝሙር 45፡6-7 በዕብራውያን 1፡8-12
እግዚአብሔር አባት እግዚአብሔር ወልድን በግልፅ የተናገረበት ቦታ ነው
ዕብራውያን 1፡8-10 ስለ ልጁ ግን፡— #አምላክ ሆይ፥ ዙፋንህ እስከ ዘላለም ድረስ ይኖራል፤ የመንግሥትህ በትር የቅንነት በትር ነው።
ጽድቅን ወደድህ ዓመፅንም ጠላህ፤ ስለዚህ እግዚአብሔር #አምላክህ ከጓደኞችህ ይልቅ በደስታ ዘይት ቀባህ፥ ይላል።
10፤ ደግሞ፡— #ጌታ ሆይ፥ አንተ ከጥንት ምድርን መሠረትህ፥ ሰማዮችም የእጆችህ ሥራ ናቸው፤
ዕብ 1:8-10
እግዚአብሔር አባት እግዚአብሔር ወልድን በግልፅ የተናገረበት ቦታ ነው
አምላክ ሆይ == የወልድ አምላክነት
ጌታ ሆይ== የወልድ ጌትነት
እግዚአብሔር #አምላክህ= የኢየሱስ ሰውነት
9) መዝሙር 110፡1#እግዚአብሔር #ጌታዬን፡— ጠላቶችህን ለእግርህ መቀመጫ እስካደርግልህ ድረስ በቀኜ ተቀመጥ፡ አለው።(ማቴዎስ 22፡43-44፤ )
እግዚአብሔር አባት ጌታ ኢየሱስን
ጌታ ጌታየን=
ያህዌ=አዶኒን
ኩርዮስ=ኩርዮስን
ዘዳግም 6 (Deuteronomy)
4፤ እስራኤል ሆይ፥ ስማ፤ አምላካችን እግዚአብሔር አንድ እግዚአብሔር ነው፤
ሮሜ 11፡33,36 የእግዚአብሔር ባለ ጠግነትና ጥበብ እውቀቱም እንዴት ጥልቅ ነው፤ ፍርዱ እንዴት የማይመረመር ነው፥ ለመንገዱም ፍለጋ የለውም።.......
ሁሉ ከእርሱና በእርሱ ለእርሱም ነውና፤ ለእርሱ ለዘላለም ክብር ይሁን፤ አሜን።
###ይቀጥላል........
የወንጌል እውነት አገልግሎት ጂማ
Gospel Truth Ministry
@wayandtruth
@wayandtruth
@wayandtruth
173 viewsDave, 14:19