Get Mystery Box with random crypto!

'ሁለቱም ጋር ሃዘን አለ፣ እስካሁን የነበረው ችግር በዚሁ ይብቃ” የኦሮሞ እና የአማራ ማህበረሰ | Wasu Mohammed(ዋሱ መሀመድ)

"ሁለቱም ጋር ሃዘን አለ፣ እስካሁን የነበረው ችግር በዚሁ ይብቃ”
የኦሮሞ እና የአማራ ማህበረሰብ ተወካዮች—ሸዋሮቢት

በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን በይፋት ቀጣና እና በኦሮሞ ብሔረሰብ ዞኖች በተፈጠረው የፀጥታ ችግር ሳቢያ ከቀያቸው የተፈናቀሉ የህብረተሰብ ክፍሎች "መንግስት ነፃነትን ያውጅልን ወደቀያችን እንገባለን" ሲሉ ጠየቁ።

ይህንን የተናገሩት ትናንት ሚያዚያ 9 ቀን 2016 ዓ.ም በኤፍራታና ግድም ወረዳ ጀውሃ ቀበሌ ላይ የአጎራባች ወረዳ ማለትም የጅሌ ጥሙጋ ወረዳ ቀበሌዎች ከከፍተኛ የመከላከያ ሰራዊት አመራሮች እና የዞን አመራሮች እንዲሁም የወረዳዎቹ አስተዳዳሪዎች ተገኝተው ባደረጉበት የምክክር መድረክ ነው።

ለበርካታ ዘመናት የኦሮሞ እና የአማራ ማህበረሰብ አብሮ ኖሯል ሲሉ ገልጸው “ከስድስት ዓመታት ወዲህ ግን ሰው በብሔሩ ተፈልጎ ሞቷል፤ ሃብት ንብረቱ ወድሟል፤ "ሁለቱም ጋር ሃዘን አለ እስካሁን የነበረውን ችግር በዚሁ ይብቃ ለአብሮነታችን በጋራ እንስራ የወደፊቱ ይበልጣ እና" በማለትም ተናግረዋል።

“አማራ ጠል አልያም ኦሮሞ ጠል የሆነ ከጭንቅላቱ ያውጣ፣ ወንድማማችነን ጎረቤት ነን በየቀያችን ሰርተን መለወጥ እንፈልጋለን” ብለዋል የሁለቱም ብሔረሰብ ተሳታፊዎች።
ቤተሰብ በቅንነት ሰብስክራይብ በማድረግ ተባበሩ       
https://www.youtube.com/channel/UCrdWHrcXNEhMfbp1ucgxd1g
አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርስዎ Join አድርገው በዚህ ይከታተሉ
https://t.me/+WNLm9dbzuIlp9DF4
https://t.me/+WNLm9dbzuIlp9DF4
ማስታወቂያና ጥቆማ መቀበያ
https://t.me/wasumohammed