2022-04-01 18:05:16
የአማራ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት የሮመዳን መልእክት
መላው ሙስሊም የሮመዳንን ፆምን ፈጣሪን በመማለድና የተፈናቀሉ ወገኖችን በመርዳት እንዲያሳልፍ የአማራ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት መከረ።
የምክር ቤቱ ሰብሳቢ ሸክ ሰዒድ መሐመድ ዛሬ ለዶይቼ ቬሌ (DW) በሰጡት መግለጫ፦ ወቅቱ በአገራችን በተለይም በአማራ ክልል ከፍተኛ መፈናቀል፣ እንግልትና የኑሮ ጉስቁልና የደረሰበት ሙስሊም ኅብረተሰብ በዚህ ቅዱስ የፆም ወር ፈጣሪ ለአገራችን ሰላም እንዲመጣ ዱዓ (ጸሎት) ማድረግ እንደሚገባ አስረድተዋል፡፡
ሼክ ሰዒድ «በሀገራችን በተቀሰቀሰዉ ጦርነት ምክንያት በርካታ ዜጎች ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው ለከፍተኛ ችግር ተዳርገዋል፣ የአካባቢ መሰረተ ልማቶችና የጤና ተቋማትና ወድመዋል፣ ከ100 በላይ መስጊዶች ወድመዋል» ብለዋል፡፡
አክለውም «በረመዳን ወር የተፈናቀሉትን ወገኖች በምግብና በአልባሳት በመደገፍ እስካሁን የተደረገውን ድጋፍ በዚህ የፆም ወቅትም አጠናክረን መቀጠል» አለብን ብለዋል። «እንዲሁም በተከሰተው የኑሮ ውድነት ምክንያት ሕይወታቸው የተመሰቃቀለውን ወገኖቻችንን ከምንጊዜውም በላይ መደገፍ፣ ከሳዑዲ አረቢያ ተመላሽ ዜጎቻችንን በገዛ አገራቸው ባየተዋርነት እንዳይሰማቸው ከጎናቸው ልንቆም ይገባል» ሲሉም ጥሪ አስተላልፈዋል።፡
የሀገራችን ችግር የሚፈታው በኢትዮጵያውያን መካከል በሚደረግ ውይይት ነው ያሉት ሸክ ሰኢድ በጫናና በዛቻ እንዳልሆነም ተናግረዋል፡፡ «በመሆኑም HR 6600 እና S 3199 የተባሉ ሰነዶችን ሁሉም ኢትዮጵያዊ በአንድነትና በቁርጠኝነት መቃወም አለበት» ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
1443ኛው ዓመተ ሂጅራ ታላቁ የሮመዳን ፆም ነገ ወይም እሁድ ይጀምራል፡፡
ዘገባ፦ ዓለምነው መኮንን፤ ዶይቸ ቬለ (DW) ከባሕርዳር
1.3K views15:05