2022-05-16 19:54:17
የሃይማኖት ንጽጽር ኮርስ
3ኛ ዙር የሙቃረናህ ደርሥ!
"ሙቃረናህ" مُقَارَنَة የሚለው ቃል "ቃረነ" قَارَنَ ማለትም "አነጻጸረ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ንጽጽር" ማለት ነው፥ ሙቃረናህ የሃይማኖት ንጽጽር"Comparative Religion" ሲሆን በእሥልምና እና በክርስትና መካከል ያለው የሥነ-መለኮት አንድነት እና ልዩነት እየተነጻጸረ የሚቀርብበት ጥናት ነው። ደርሡ (ትምህርቱ) የሚፈጀው 6 ወር ኢንሻሏህ ሲሆን ሁለት ተርም አለው።
፨ የመጀመሪያው ተርም ዐጽመ-አሳብ በፈጣሪ እሳቦት ላይ የሚያውጠነጥኑ ሲሆኑ የሚከተሉት ናቸው፦
ምዕራፍ አንድ
ሥላሴ"trinity"
ምዕራፍ ሁለት
ነገረ-ክርስቶስ"Christology"
ምዕራፍ ሦስት
ነገረ-ማርያም"Mariology"
ምዕራፍ አራት
ነገረ-መላእክት"angelology"
ምዕራፍ አምስት
ነገረ-ምስል"Iconlogy"
፨ የሁለተኛው ተርም ዐጽመ-አሳብ በቅዱሳን መጽሐፍት ላይ የሚያውጠነጥኑ ሲሆኑ የሚከተሉት ናቸው፦
ምዕራፍ አንድ
አህሉል ኪታብ"People of the Book"
ምዕራፍ ሁለት
መጽሐፍት"scriptures"
ምዕራፍ ሦስት
የመጽሐፍ አጠባበቅ"preservation"
ምዕራፍ አራት
የመጽሐፍት ልኬት"Standardization"
ምዕራፍ አምስት
የባይብል ግጭት"Contradiction"
ምዕራፍ ስድስት
ኦሪት"Torah"
ምዕራፍ ሰባት
ወንጌል"Gospel"
ደርሡ በሳምንት አንዴ የሚለቀቅ ሲሆን በሁለት ሳምንት አንዴ የሁለቱ ሳምንት ጥያቄ ፈተና ይኖራል። ፈተናው ከ 10 የሚወሰድ ሲሆን ከ 6-10 ማምጣት ይጠበቅባችኃል። ከ 6 በታች ሦስት ጊዜ ካመጣችሁ በሰርተፍኬት አናስመርቅም።
የሙቃረናህ ደርሥ ቦርድ አባላት አሥር ሲሆኑ ዋና ዋናዎቹ አራት ናቸው፥ እነርሱ፦
1. ወንድም ወሒድ የደርሡ አስተማሪ፣
2. እኅት ሐደል የደርሡ አቅራቢ፣
3. እኅት ሐናን የደርሡ ፈተና አርቃቂ
4. ወንድም መህዲይ የደርሡ ፈታኝ እና ውጤት ክፍል ናቸው።
ለመመዝገብ ከታች የተዘረዘሩት የቦርዱ አካላት በውስጥ ያናግሩ!
እኅት ሐድልን፦ https://t.me/Ohanw9
እኅት ረምላን፦https://t.me/REMLANEG
እኅት ሰላምን፦ http://t.me/Selam9S
አኅት ዘሃራን፦ https://t.me/Zhara_mustefa
እኅት ሐቢባን፦ https://t.me/Mahbubo
እኅት አበባ፦http://t.me/temariwa_lji
ቦታ ሳይያዝ ይመዝገቡ! መልካም የትምህርት ጊዜ ይሁንልዎ!
ወጀዛኩሙሏህ ኸይራ!
6.2K viewsFu Ne, 16:54