2022-06-16 17:54:25
እውነተኛ ፍቅር
ክፍል
ከሻም ጉዞ መልስ ከድጃ (ረዐ) ለሙሀመድ (ሰዐወ) "ለአንተ እኔ ዘንድ ጥሩ ደስታና ስጦታ ተቀምጦልሀል ከሁሉም ሰራተኞች የበለጠ እጥፍ ተጨማሪ ገንዘብ ይከፈልሀል" አለችው፡፡ ሙሀመድም (ሰዐወ) ከጉዞ መልስ አጎቱ ጋር ተመለሰ፡፡ አቡጣሊብም አባት ለልጅ አቀባበል ከሚያደርገው በላይ በደስታ ተቀበሉት፡፡ ከዚያም እንዲህ አሉት
"ልጄ ሆይ ከድጃ ከፈለችህ"
ሙሀመድም "ከውሉ በተጨማሪ ትርፍ ገንዘብ ጨምራ እንደምትሰጠኝ ቃል ገባችልኝ " አለ
አቡጣሊብም "ልጄ ሆይ የወላጆችህ አደራ አለብኝ እንደምታዬኝ አርጅቻለሁ የሞትም ምልክቱ እየታየብኝ ነው ስለዚህ አንተን ድሬ ወግ ማዕረግህን ማየት እፈልጋለሁኝ እናም ከቁረይሾች ጥሩ ሚስት ብፈልግልህና ብድርህስ " አሉ፡፡
ሙሀመድም "አጎቴ ሆይ አንተ እንደፈለክ ማድረግ ትችላለህ እኔ ያንተን ትዕዛዝ ለመፈፀም ዝግጁ ነኝ " አለ፡፡
ከሻም መልስ በሁለተኛው ቀን ታላቁ ሙሀመድ (ሰዐወ) ገላቸውን ታጥበው አቡጣሊብ በገዙላቸው ልብስ ተውበው ወደ ከድጃ ሄዱ፡፡ ከድጃም እውነተኛ ፣ ታማኝ ፣ ፍትሀዊ ፣ አዛኝ ፣ መልካም ሰሪን ታላቁን ወጣት በውበቱ ላይ አዲስ ልብስን ተጎናፅፎ ስታየው ተደነቀች ከዚያም "እንዲህ አምረህ የመጣኸው ከኔ አንድ ነገር ፈልገህ ሳይሆን አይቀርም ምን ልታዘዝ ሀጃህ ምንድነው?" አለችው፡፡
"ከአንቺ ዘንድ ያለኝን ገንዘብ ፈልጌ ነው " አላት፡፡
"መሀመድ ሆይ ይህ ውዐትና ገንዘብ ይዘህ በንደዚህ ሁኔታህ ምን ልትሰራበት ነው" አለችው፡፡
"አጎቴ ከቁረይሽ የሆነችን ሚስት እድርልሀለው ስላለኝ ተስማምቼ ነው የመጣሁት " አላት፡፡
"ሚስት ልታገባ አስበህ ከሆነ እኔ እጅግ ቆንጆ የሆነች ገንዘብ ያላት ለዘርህ ቅርብ የሆነች ሹማምንቶች ለጋብቻ ጠይቀዋት እንቢ ያለች በሰዎች ዘንድ የተከበረች አዕምሮዋ የተረጋጋና የሞላ አንተን እንጂ ከአንተ ምንም የማትፈልግ ሚስት አዘጋጅቼልሀለው፡፡" አለችና እንዲህ ስትል ቀጠለች "ከአንተ የማልደብቀው ሁለት ነውር አላት አንደኛው ነውሯ አግብታ ታውቃለች ሁለተኛው በዕድሜ ከአንተ ትበልጣለች " አለች፡፡
መሀመድም "አንቺ ጥሩዋ ሴት ሆይ ማናት እሷ የትስ ነው ያለችው " አላት
"ያንተ ምርኮኛ ናት እዚሁ ቅርብ አጠገብህ ታያታለህ ስሟም ከድጃ ይባላል" አለችው፡፡
መሀመድም ሁሉም ነገር በተገለጠለት ጊዜ ምንም መልስ ሳይሰጥ ዝም አለ፡፡
ከድጃም "የእሺታ መልስ ስጠኝና ልቤን አሳርፈው" አለችው፡፡
አሁንም ከወጣቱ መልስ ስታጣ "አላህ ካለ እኔ ከታጋሾች ሆኜ ታገኘኛለህ አንተንም በምንም አልወነጅልህም" አለች፡፡
መሀመድም (ሰዐወ) "ከድጃ ሆይ አንቺ የተከበርሽና ባለብዙ ሀብት እኔ ደግሞ የአንቺ ተቀጣሪና ከምትሰጪኝ ገንዘብ ሌላ ምንም የለኝም እናም ገንዘብ የሌለው ፈልጎም ቢሆን ቢጤውን ያገባል" አላት፡፡
...ከድጃም እንዲህ አለችው "ገንዘቡን ብናደባልቀው ይበዛል እንጂ አያንስም"፡፡ ወጣቱም በድጋሚ ምንም ሳይመልስላት ዝም አለ፡፡
ከድጃም "በግልፅም ሆነ በድብቅ የሚሰሩትን የሚያውቅና የሚያይ በሆነው ጌታዬ ይሁንብኝ በኔ በኩል ምንም የሚሸፍነው ነገር የለም፡፡ ሁሉም ነገር እውነት ነው በል አሁን ወደ ቤተሰቦችህ ሂድና አጎትህን ለጋብቻ እንዲጠይቁኝ ንገራቸው፡፡ ምናልባት አባቴ ብዙ ገንዘብ ለኒካህ ከጠየቃቸው የጠየቀውን በሙሉ እኔ እሰጥሀለው፡፡ እኔ ያንተ ነኝ እኔው መረጥኩህ ከአንተ ሌላ ማንንም አልፈልግም፡፡ ልቀርብህ ሳስብ አትራቀኝ " አለችው ልመና በተቀላቀለበት አነጋገር፡፡
መሀመድ (ሰዐወ) ተነስቶ ከቤቷ ወጣ፡፡ ከድጃ መሀመድ (ሰዐወ) ከመምጣቱ በፊት ለወዳጅ ጓደኛዋ ለነፊሳ አጫውታት ነበር፡፡ ነፊሳም እሱን አሳምና ከምትወደው ሰው ጋር እንደምታጋባት ቃል ገብታላት ነበር፡፡ ወጣቱ መሀመድና ነፊሳ ሲገናኙ ነፊሳ ስለታላቋ ሴት ስለ ከድጃ መልካም ባህሪና እንዲሁም እሱን ማግባት እንደምትፈልግ ከገንዘቧ እንደምታስበልጠው አንድ በአንድ ነገረችው፡፡ ጥያቄዋን እንዲቀበልም አሳመነችው፡፡
ታላቁ ሰው አጎቱ ቤት ተመለሰ፡፡ አቡጣሊብን ከወንድሞቻቸውና እህቶቻቸው ጋር ቤት ቁጭ ብሎ አገኛቸው፡፡ አጎትዬው በፈገግታ ተቀበሉት ከዚያም "ከድጃ ከከባድ ስጦታ ጋር እንደላከችህ እገምታለው" አሉት፡፡ መሀመድም "አጎቴ ሆይ ግምትህ ትክክል ነው፡፡ ከአንተ ጉዳይ አለኝ " አለ፡፡
አቡጣሊብም "ከአንተ ጉዳይ ጀርባ ጌታህ አለ፡፡ ለመሆኑ ምንድናት ጉዳይዋ" አሉት፡፡
መሀመድም "ሂዱና ከድጃን ለትዳር እንደምፈልጋት ቤተሰቧን ጠይቁና አምጡልኝ " አለ፡፡
የመሀመድ አጎቶች ተያዩ ከአቡጣሊብ በስተቀር ማንም ምንም መናገር አልፈለገም፡፡ አቡጣሊብም "ልጄ ሆይ ከድጃ እጅግ የተከበረችና በሰዎች ዘንድ የተወደደች ብዙ ሀብት ያላት ከአሁን በፊት ሁለት ሰዎች አግብታና በሞት የተለዩዋት ንብረታቸውን ወርሳ የምትኖር አሁን በቅርቡ ታላላቅ ሹማምንቶች ለጋብቻ ጠይቀዋት እንቢ ያለች ናት፡፡ አንተ የወንድሜ ልጅ ደግሞ ምንም ንግድ የለህም የርሷ ተቀጣሪ ነህ፡፡ ስለዚህ ራሷን አሳልፋ አትሰጥህም" አሉት፡፡
ሙሀመድም (ሰዐወ) "አጎቴ ሆይ አሁን ያልከውን በሙሉ አውቀዋለሁ እረዳሀለው የጋብቻ ጥያቄው ግን ከራሷ ነው የመጣው፡፡ " አላቸው
.
.
ይቀጥላል ኢንሻ አላህ
@tualibelilm
644 views14:54