#* *#1 ያለፉ ፈገግታዎች . . . /እኔን ብሎ ርዕስ ሰጪ / የማር ጠብታ ምታክል ሩቢ ወደኔ ድክ ድክ ትላለች. , አቀፍኳት . . . እሩቅ አልመስልህ አለችኝ ማውቀው አይን. . . በዘመኔ እርቀት የማይጨልምብኝ ፍክት ያለ ገፅ . . . ትንንጥ ጣቶቿን በየተራ ሳምኳቸው . . . "ማነው ሽምሽ. . ." አይኗቿ ተንከራተቱ . . . ስሟ በዝቶባት ነው ብዬ ገመትኩ . . .. የቱን እንደምትነግረኝ ግራ ገብቷት መሰለኝ . . .ወይ አታውቀውም . .. . . ፈተናዋ የሷን አለማወቋ ብቻ አይደለም የአባቷንም ነው ብዬ አሁንም ገመትኩ . . . "እናትሽ የታለች . . ." ፈለገቻት . .. አልታየቻትም አሰብኩ. . . የቱ ነው ከባዱ የህይወት ምዕራፏ.. . አሁኗ ወይስ በኋላዋ ? ትናንሽ ነፍሶች ምርጫ የላቸውም. . . ከዝናቡ መርከፍከፍ በሱም መራስ ወይስ ሙቅ ፍራሽ ተብለው አልመረጡም ወላጅ ሳይፈጥራቸው በፊት የመረጠውን ለመኖር ይገደዳሉ . . . እምቡጥ የወይን ፍሬ የመሰለ እግሯ ጫማ የለውም ከመሬቱ እርጥበት ጋር ተስማምተዋል ፣ ለመክዳት ጥቂት ሰበበ የሚፈልጉ ጨርቆች እዛም እዚህ አካላቷ ላይ ተበታትነዋል ፣ ከእግዜር ካፍያ በስተቀር በሰው እጆች ያልታጠበ ፀጉሯ በግንቦት ፀሃይ እንደተኮማተሩ ቅጠሎች ደክሞዋል. . .፣ ከሚያውቁት ደረቅ ጡት ጋር የታገሉ ከንፈሮቿ ብሶተኛ የጨለማ አበቦች ይመስላሉ፤ ሆዷ በእንቁልልጭ መመገብ ለምዷልና ላለማልቀስ እንደሚቀምስ ያስታውቃል. . . ብዙ ብዙ ብዙ የማታውቃቸው ስቃዬች አሏት ምን አልባት ለነገ ያሴሩባት. . . . ከዝች ትንጥዬ ነፍስ ውስጥ የሚነፍሰው ብቸኛ ነገር ፍልቅልቅ ልጅነት ብቻ ነው . . ያልገባትን የምትኖር የበርሃ አደይ . . . የበርሃ ምንጭ . .. "ኑኑ . . . " ወደጠራት ድምፅ ከመሄዷ በፊት እጇን ዘረጋችልኝ . . . "ባቦ. . " አለችኝ ጆሮን ሰርስሮ ልብን በሚያቃጥል ጥንጥዬ አንደበት የጠራትን ማንነት ለማየት ዙርያዬን ቃኘው ለሷ ብር መስጠት ጨዋነት አልመስልክ ብሎኝ. . ርሃብ ግዴታው በሆነ የሰው ዘር ፊት ጨዋነት ሚለውን እቃቃ ለመጫወት ያፈረ አእምሮ አልነበረኝም /ምን አልባትም ጭራሱኑ የለኝም / ኪሴ ውስጥ የነበሩትን ገንዘቦች ጥቅልል አረኩና "ይኼን ለማማ ብቻ ስጭያት እሺ" "እሲ ናልያም ትስት" ብላኝ ከእቅፌ ብን ብላ በረረች. . .. ለሽርፍራፊ የደቂቃ ግማሾች ከቦታው ላይ ተከዝኩ. . መኪናዬ ውስጥ ገብቼ ወደፊት ሳዘው ወደኋላ የቀረ እኔ ነበረ. . . ተመለስ ሚለኝ "ኑኑ" የሚል ሙቅ ድምፅ . . በተስፋ መቁረጥ የምትጣራ ለስላሳ እናት . . . . . የት ይሁን ይኼን ድምፅ ማውቀው . . . ? የት ቦታ ? መኪናዬ ወደፊት እኔ ወደኃላ . . ... /ትዝታ/ | ❀:✧๑♡๑✧❀| @tiztawe @tiztawe ೋ•✧๑♡๑✧•ೋ 1.4K viewsedited 17:06