ታዳጊዎቹ የድረ-ገፅ አበልፃጊዎች ጎዶሊያስ ሙሉጌታ እና ሰላዲን መራዊ በአቤም ዩዝ አካዳሚ የሰባተ | Tikvah-University
ታዳጊዎቹ የድረ-ገፅ አበልፃጊዎች
ጎዶሊያስ ሙሉጌታ እና ሰላዲን መራዊ በአቤም ዩዝ አካዳሚ የሰባተኛ ክፍል ተማሪ ናቸው።
ታዳጊዎቹ የግለሰብ መረጃን ወይም 'CV' የሚያደራጅ ድረ-ገፅ አበልፅገዋል።
ድረ-ገፁ፤ ሰዎች ሥራን ለመቀጠር የሚያስገቡት የራስ መግለጫ 'CV'' በእጅ ስልካቸው ላይ እንዲያገኙና በማንኛውም ሰዓት ለሚፈልጉት ቀጣሪ ማስገባት የሚያስችል ነው።
ድረ-ገፁ የግለሰቡን የትምህርት ደረጃ፣ አድራሻ፣ ክህሎቶች እና የሰዎችን ምስክርነትን ማካተት የሚያስችል መሆኑን ታዳጊዎቹ ተናግረዋል።
ድረ-ገፁ የሰዎችን ብቻ ሳይሆን የድርጅቶችን መረጃ እንዲያስቀምጥ ተደርጎ የተዘጋጀ መሆኑንም ታዳጊዎቹ አስረድተዋል።
ታዳጊዎቹ በአዲስ አበባ ሳይንስ ሙዚየም በተከፈተው የ'ስታርት አፕ' አውደ-ርዕይ ላይ ፈጠራቸውን አቅርበዋል። #ENA
@tikvahuniversity