በአዲስ አበባ በ9 ወራት 286 ሰዎች በመንገድ ትራፊክ ግጭት ህይወታቸውን አልፏል ተባለ በአዲስ አበባ በ9 ወራት ውስጥ 286 ሰዎች በመንገድ ትራፊክ ግጭት ህይወታቸውን ማጣታቸውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንገድ ደኅንነት ምክር ቤት የ2016 በጀት ዓመት የ9 ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት አመለከተ፡፡ በተጠቀሰው ጊዜ 716,624 የትራፊክ የደንብ ጥሰቶች መፈጸቸው ሲገለፅ ፣ ምንም እንኳን ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ 9 ሰው ሞት ቢቀንስም በተለይ የትራፊክ አደጋው አምራች የሆነውን ወጣቱን ሀይል እያሳጣ መሆኑ ተጠቁሟል። @TikvahethMagazine 22.7K views09:57