Get Mystery Box with random crypto!

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት  አቶ ጌታቸው ረዳ ከ ' ቢቢሲ ፎከስ ኦን አፍሪካ ' ጋር | TIKVAH-ETHIOPIA

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት  አቶ ጌታቸው ረዳ ከ ' ቢቢሲ ፎከስ ኦን አፍሪካ ' ጋር ቃለ ምልልስ አድርገው ነበር።

በቃለምልልሱ ፥ ባለፉት ሳምንታት በአማራ እና ትግራይ አዋሳኝ አካባቢዎች የነበረው ግጭት በ " የሚሊሻ አባላት " መካከል እንጂ መደበኛ ኃይሎች የተሳተፉበት አልነበረም ብለዋል።

" አማራ ክልል በኩል የነበሩ ሚሊሻዎች የተለያዩ አስጊ እንቅስቃሴያዎችን ሲያደርጉ ነበር። በእኛ በኩል ያሉ የሚሊሻ አባላት ምላሽ ሰጥተዋል " ሲሉ ገልጸዋል።

የአማራ ክልል ያወጣውን መግለጫም  " መሬት ላይ ያለውን እውነታ ያላገናዘበ " ብለዋል።

የሰላም ስምምነቱ #ተፈጻሚ_እንዳይሆን እያደረገ ያለው " ሕጋዊ የልሆነ የአማራ አስተዳደር ነው " ሲሉ ተደምጠዋል።

አቶ ጌታቸው በዚሁ ቃለ ምልልስ ፥ በሰላም ስምምነቱ መሰረት በጦርነት ምክንያት የተፈናቀሉትን ሰዎች ወደ ቀያቸው እንዲመለሱ ከስምምነት መደረሱን አስታውሰዋል።

" ሕጋዊ ያልሆኑ አስተዳደሮችን ለማፍረስ ከፌደራል መንግሥቱ ጋር አብረን እየሠራን ነው። ከአማራ ክልል ጋርም ቢሆን በተወሰነ ደረጃ አብረን እየሠራን ነው " ብለዋል።

" የፕሪቶሪያው ስምምነት ተፈጻሚ እንዳይሆን የሚሹ አካላት እንዳሉ ግን በጣም እርግጠኞች ነን " ሲሉ ተደምጠዋል።

አቶ ጌታቸው እነዚህ አካላት እነማን እነደሆኑ በግልጽ በስም ጠርተው አልጠቀሱም።

#BBC #FocusonAfrica

@tikvahethiopia