Get Mystery Box with random crypto!

TIKBAH-ETH

የቴሌግራም ቻናል አርማ tikbahethiopia — TIKBAH-ETH T
የቴሌግራም ቻናል አርማ tikbahethiopia — TIKBAH-ETH
የሰርጥ አድራሻ: @tikbahethiopia
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 4.57K

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-05-28 07:40:41
ጋዜጠኛ በቃሉ አላምረው በቁጥጥር ስር ዋለ።

ከጥቂት ወራት በፊት ታስሮ ከእስር የተፈታው የቀድሞ የአውሎ ሚዲያ ባልደረባ አሁን ላይ " አልፋ ቲቪ " የተሰኘ የማህበራዊ ሚዲያ መስራች እና አዘጋጅ ጋዜጠኛ በቃሉ አላምረው በፀጥታ ኃይሎች ቁጥጥር ስር መዋሉን ጠበቃ ታደለ ገብረመድህንን ዋቢ አድርጎ አዲስ ስታንዳር አስነብቧል።

የጋዜጠኛውን መታሰር ባለቤቱ ሄለን አባተ አረጋግጠዋል።

በሌላ በኩል ፤ ትላንት የፊንፊኔ ኢንተግሬትድ ብሮድካስቲንግ የቴሌቪዥን ጣቢያ ጋዜጠኛ ሰቦንቱ አህመድ በአዲስ አበባ ፖሊስ ቁጥጥር ስር የዋለች ሲሆን (በለቡ ፖሊስ ጣቢያ ነበረች) ዛሬ ወደ ቢሾፍቱ መወሰዷን የጣቢያው ዋና ዳይሬክተር ለሚ ታዬ መናገራቸውን ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ድረገፅ አስነብቧል።

ሰቦንቱ ትላንት በፖሊስ የተያዘችው አመሻሽ ላይ ከስራ ቦታዋ ስትወጣ ሲሆን በቁጥጥር ስር ያዋሏት ፖሊሶች የፍርድ ቤት ትዕዛዝ አለመያዛቸውንም ዋና ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል።

አክለውም፤ ትላንት ለቡ ፖሊስ ጣቢያ እያለች አነጋግረዋት እንደነባርና የተያዘችበት ምክንያት ምን እንደሆነ እንዳልተገለጸላት ፍርድ ቤትም እንዳልቀረበች ለ " ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ድረገፅ " አስታውቀዋል።

ጋዜጠኛዋ ዛሬ ወደ ቢሾፍቱ ከተማ እንድትወሰድ ተደርጓል።

@tikvahethiopia
2.3K views04:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-28 07:40:40
" Galatoomaa Tour "

የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ) ተቀዳሚ ምክትል ሊቀመንበር አቶ በቀለ ገርባ እና የፓርቲው ምክትል ሊቀመንበር አቶ ጃዋር መሀመድ ወደ በሰኔ እና ሃምሌ ወር 2022 ወደ #ሰሜን_አሜሪካ እና #አውሮፓ እንደሚጓዙ ታውቋል።

አመራሮቹ ጉዟቸውን " Galatoomaa Tour " በሚል የሚያደርጉ ሲሆን በተለያዩ ከተሞች ከደጋፊዎቻቸው ጋር ይገናኛሉ ተብሎ ይጠበቃል።

ጉዞውን በተመለከተ እስካሁን በሁለቱ ወራት የሚያዳርሷቸውን ከተሞች እና ቀናት ይፋ ከመሆን በዘለለ ለጊዜው በዝርዝር ይፋ የተደረገ መረጃ የለም።

@tikvahethiopia
1.9K views04:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-28 07:40:40
#EHRC

ትላንት በቁጥጥር ስር የዋሉት ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ እና ጋዜጠኛ ያየሰው ሽመልስ አጠቃላይ እስካሁን በቁጥጥር ስር የዋሉ ጋዜጠኞች / የሚዲያ አካላትን ቁጥር 16 አድርሶታል።

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለ ፥ " የሚዲያ ባለሙያዎች መታሰራቸው ከመገናኛ ብዙሃን ህጉ ጋር የሚጻረርና መዘዙ ከመገናኛ ብዙሃን እና ሃሳብን ከመግለጽ የዘለለ በመሆኑ አሳሳቢ ነው " ብለዋል

ከመገናኛ ብዙሀን ህግ ጋር በተጻራሪ ከፍርድ በፊት ረዘም ላለ ጊዜ አስሮ ማቆየት፣ ታሳሪዎች ያሉበትን ቦታ አለመግለጽ እና መደበኛ ባልሆነ እስር ቤት ማሰር ሁኔታውን እንደሚያባብስ በመግለፅ ሁሉም የሚዲያ አካላት በአስቸኳይ ከእስር እንዲፈቱ ጠይቀዋል።

ዶ/ር ዳንኤል በቀለ ኮሚሽኑ ሁኔታውን መከታተሉን እንደሚቀጥልም አሳውቀዋል።

@tikvahethiopia
1.6K views04:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-28 07:40:40 #ፌዴራል_ፖሊስ_ወንጀል_ምርመራ

የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ የኦፕሬሽን ዋና መምሪያ ኃላፊ ሙሊሳ አብዲሳ የሰጡት ማብራሪያ ፦

" ህግ ማስከበር ሲባል ብሄርን አይለይም፤ ሃይማኖትን አይለይም ፤ የፖለቲካ status አይለይም ፤ የሚዲያ አክቲቪስት ማንም ማንም ይሁን የSocial Status ፣ ሃይማኖቱ ምንም መሰረት አያደግም።

ህግ ለሁሉም እኩል ነው። እንደ ፖሊስ ሞያዊ ነፃነቱን ጠብቀን የምርመራ ስራ ጥቆማ ሲደርሰን በየትኛውም አካል ላይ ህግ የማስከበር ስራ እየተሰራ ነው የሚገኘው።

እንደሚታወቀው በአሁን ሰዓት ብዙ የሚዲያ ተከታይ ያላቸው ሰዎች ብሄርን ከብሄር የሚያጋጩ፣ ሃይማኖትን ከሃይማኖት የሚያጋጩ ፣ ጥርጣሬን የሚፈጥሩ የህዝቦቻችንን ፣ አጠቅላይ የኢትዮጵያን ህዝብ አብሮነት የሚፈታተኑ እነሱ ጥቅም የሚያገኙበትን በሚዲያ ዘመቻ የሚያደርጉትን በሽብር ድርጊት ውስጥ የተሳተፉትን ሰዎች በማስረጃ ላይ ሆነን መረጃ በመሰብሰብ በህግ ቁጥጥር ስር በማዋል ወደ ህግ እያቀረብን ነው።

ስለዚህ የሆነ ሚዲያ ወይ ጋዜጠኛ የሆነ ምንም ቢሆን እንደ defense ሊቀርብ አይችልም። በወንጀል ውስጥ የተሳተፈ መረጃ የተገኘበት ማንኘውም ሰው ላይ እርምጃ ይወሰዳል፤ በህግ ይጠየቃል፤ ግልፅ በሆነ ነፃ በሆነ ፍርድ ቤት አቅርበን ምርመራ ስራ እንሰራለን።

ስለዚህ በአሁን ሰዓት የሚዲያ ስራ ላይ የተሳተፉ ሰዎች እሱን እየተጠቀሙ አጠቃላይ stability እንዳይኖር የሆነ title እየሰጡ እንደ ገቢ ምንጭ የኢትዮጵያ ህዝብ ያልተረዳው ነገር እነኚህ አክቲቪስት የተባሉ ታሰሩ የተባሉ ግለሰቦች እንደ ገቢ ምንጭ የሚጠቀሙት አይነት ነው ያለው።

በምርመራ እንዳገኘነው አንድ ግለሰብ ከ4 ዩትዩበሮች ጋር ውል አስሯል፣ ከአንዱ ዩትዩበር 25 ሺህ ብር ነው የሚከገለው በአንድ ጊዜ እስከ 100 ሺህ ነው የሚከፈለው፤ ይሄን ለማድረግ ተመልካች እንዲያገኝ ለማድረግ ብሄርን ከብሄር የሚያጋጭ፣ ሃይማኖትን ከሃይማኖት የሚያጋጭ ፣ ወይም የመንግስትን ተቋም ፣ ወይም የመንግስትን ተሿሚዎች በሚያሸማቅቅ መልኩ ግልፅ በሆነ መልኩ characterize በማድረግ title እየሰጡ እንዲህ እያደረጉ ተመልካችን፣ like , share በብዛት እንዲያገኙ ብዙ ነገር በማድረግ ይሄን መሰረት በማድረግ destabilize በማድረግ የተለያዩ የወንጀል ድርጊቶችን፣ የሃሰት የውሸት ፕሮፖጋንዳዎችን በመልቀቅ ህዝቦች አብረው እንዳይኖሩ ሀገሪቱ በሰላም ተረጋግታ እንዳትኖር አጠቃላይ የማወክ ስራ እና ጥርጣሬ በሚፈጥር መልኩ ጥላቻን በውሸት ዘመቻ እያደረጉ ህዝቡ ላይ ይሄን እየጫኑ ለራሳቸውን የገቢ ምንጭ አድርገው ሀገሪቷን አደጋ ላይ ለመጣይ የሚሰሩ አካላት ናቸው በቁጥጥር ስር የዋሉት።

ይሄንን ደግሞ ፖሊስ ህግን መሰረት በማድረግ ፍርድ ቤት በማቅረብ የጊዜ ቀጠሮ በመጠየቅ በራሳቸው ፍላጎት በሚፈልጉት ጠበቃ ተወክለው በቤተሰቦቻቸው እየተጠየቁ ይሄን የምርመራ ስራ ፣ የህግ ማስከበር ስራ በደንብ እየተሰራ ነው።

ስለዚህ በአጠቃላይ ማንኛውም ሰው ከህግ በታች ነው።

ከህግ በታች እስከሆነ ድረስ ጥቆማ የቀረበበትን እንደፖሊስ ሙያን መሰረት አድርጎ የህግ የማስከበሩን ስራ ማንኛውም ሰው ላይ በየትኛውም ላይ ብዙ እሱን የሚከተል ሰው ሊኖር ይችላል ከዚህ በፊት እንደተደረገው ፣ የሃይማኖት ሰው ሊሆን ይችላል፣ ማንኛውም ሰው ሊሆን ይችላል ዋናው መሰረት የህግ ስህተት አለ ? ወይስ የለም ? የሚለው ነው። ስለዚህ እስካሁን ሃሳብን በነፃነት የመግለፅ ስም ብዙ ነገሮች ተችለዋል በአሁን ሰዓት ግን የለየለት የሽብር ስራ ፣ የሽብር ፈጠራ ፣ ሀገርን የማፍረስ ስራ ፣ ህግ የሌለ እስከማስመሰል ፣ የፍትህ ተቋማት እርምጃ መውሰድ አይችሉም የሚያስብል ደረጃ ላይ ደርሶ ሀገርን የማፍረስ ተልዕኮ ላይ እየሰሩ ያሉት አካላት ላይ የህግ የበላይነት ለማስከበር ከምን ጊዜውም በላይ የፌዴራል ፖሊስ ከሌሎች የፍትህ ተቋማት ጋር በመሆን የምርመራ ስራን እየሰራ ይገኛል። "

@tikvahethiopia
1.4K views04:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-28 07:40:40
#Update

የ " ፍትህ መጽሔት " ማኔጂግ ዳሪክተር ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ " የሀገር መከላከያ ሰራዊትን በህዝብ ዘንድ አመኔታ ለማሳጣትና ሁከትና ብጥብጥ በማስነሳት ወንጀል " መጠርጠሩን መርማሪ ፖሊስ ዛሬ ለፍ/ቤት ገልጿል።

ፖሊስ ጋዜጠኛ ተመስገን በተጠረጠረበት ሁከትና አመጽ ማስነሳት ወንጀል በምስክር ለማስመረጥና የምስክር ቃል ለመቀበል ተጨማሪ ማስረጃ ለመሰብሰብ እና የምርመራ ስራውን አጠናክሮ ለመቅረብ 14 ተጨማሪ የምርመራ ቀናት እንዲሰጠው ችሎቱን ጠይቋል።

የጋዜጠኛ ተመስገን ጠበቃ ሄኖክ አክሊሉ መከላከያን መተቸት እምነት ማሳጣት አለመሆኑን ጠቅሶ ተከራክሯል።

በምስክር ማስመረጥ ለተባለውም ቢሆን ተመስገን አገር የሚያውቀው በመሆኑ ማስመረጥ ጥያቄው ተገቢ እንዳልሆነ ገልጿል።

ጠበቃው አክሎም ጋዜጠኛ ተመስገን የሚሰራበት ሚዲያ ፍቃድ ያለው ህጋዊ ተቋም እንደመሆኑ ወንጀል ሰራ እንኳ ቢባል በመገናኛ ብዙሃን አዋጅ እንጂ በጊዜ ቀጠሮ ሊጠየቅ እንደማይገባ ተከራክሯል።

ፖሊስ በዩቱዩብ ቃለመጠይቅ እያደረገ ከሌሎች አካላት ጋር ሁከትና አመጽ የማነሳሳት ስራ እየሰሩ ነው ሲል ባቀረበው የመነሻ ምርመራ ሪፖርትን በተመለከተ ጋዜጠኛ ተመስገን ከ4 አመት ወዲህ ምንም አይነት ከማንም ጋር ቃለመጠየቅ እንዳላደረገ ጠበቃ ሄኖክ አብራርቷል።

 በሚሰሩበት ሚዲያ የሀገር መከላከያ ተቋምም ቢሆን ተተችቻለው በህዝብ ዘንድ እምነት አጣሁ ብሎ አለመቅረቡን  ጠቅሰው ቢቀርብ በመገናኛ ብዙሀን አዋጅ መሰረት በሚሰራበት ሚዲያ ማስተካከያ ከማድረግ እንደማይታለፍ መከራከሪያ ነጥቡ ጠቅሷል።

ያንብቡ
https://telegra.ph/Tarik-Adugna-05-27

ምንጭ፦ ጋዜጠኛ ታሪክ አዱኛ

@tikvahethiopia
1.5K views04:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-12 20:37:48
#ትኩረት

የሰሜን ወሎ፣ ደቡብ ወሎና ከሚሴ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ ፤ " የዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ወደ ቅዱስ ላልይበላ ዓለም አቀፍ ቅርስ ሊመለከት ይገባል " ሲሉ ጥሪ አቀረቡ።

ብፁዕነታቸው ቅዱስ ላልይበላን በማስመልከት ዛሬ በተሰጠ መግለጫ በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ እና በነበረው ጦርነት የቅዱስ ላልይበላ ቅርስ የቱሪዝም እና የከተማው እንቅስቃሴ ከፍተኛ ጫና ውስጥ መውደቁን ገልጸዋል፤ በዚህም አገልጋዮች ለከፍተኛ ችግር መጋለጣቸውን አሳውቀዋል።

ቅዱስ ላልይበላ የሁሉም ኢትዮጵያዊ ሐብት እንደመሆኑ አቅም በፈቀደ ኢትዮጵያዊ የሆነ ሁሉ ለድጋፍ እጁን እንዲዘረጋ ጥሪ አቅርበዋል።

ብፁዕነታቸው ሁለችንም የድርሻችንን በመወጣት ቅርሳችን እንጠብቅ ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

ዜጎች ድጋፋቸውን በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፣ አቢሲኒያ እና ዳሽን ባንኮች በ 0712 የባንክ የሒሳብ ቁጥር ማድረግ ይችላሉ።

ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 0911061164 እና 0913912457 መደወል ይቻላል።

ምንጭ፦ የኢኦተቤ ህዝብ ግንኙነት

@tikvahethiopia
3.8K views17:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-12 17:55:26
ቀይ መስቀል ድጋፍ እያደረገ ነው።

የደቡብ ኦሞ ዞን ቀይ መስቀል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በቶልታ፣ መጸርና በርካ ለተፈናቀሉ ዜጎች ድጋፍ አፍርጓል።

የሰሞኑን ፀጥታ ችግር ተከትሎ በደቡብ አሪ ወረዳ መፀር፣ ቶልታና በርካ አካባቢዎች ከፍተኛ የቤት ቃጠሎና የንብረት ውድመት የተከሰተ ሲሆን ነዋሪዎቹም ከስፍራው ሸሽተዋል፡፡

ራሳቸውን ለማዳን በሐይማኖት ተቋማት፣ በትምህርት ቤቶችና በፖሊስ ጣቢያዎች የተጠለሉት የማኅረሰቡ አካላትን የደቡብ ኦሞ ዞን ቀይ መስቀል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ከራሱና ማኅበረሰቡን በማስተባባር የዕለትና ሌሎችንም ድጋፍ ለመስጠጥ ችሏል፡፡

የተደረገው ድጋፍ ፦ ለሶስቱም አካባቢዎች ለበርካ፣ ቶልታና መፀር 130 ደርዘን እሽግ ውሃ፣ 3 ሺህ ዳቦ፣ 50 አገልግል እንጀራ፣ 10 ኩንታል ሞኮሮኒ፣ 2 ኩንታል ሩዝ፣ 6 ኩንታል ነጭ ዱቀት፣ 2 ኩንታል ጤፍ፣ 18 ደርዘን ጁስ፣ 6 ደርዘን ብስኩት እና ሌሎችም ይገኙበታል።

አሁንም ድጋፉን ለማጠናከር ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ ቀይ መስቀል ጥሪ አቅርቧል፦ ችግር ላይ የወደቁ ወገኖችን ለማገዝ በገንዘብ ድጋፍ ለማድረግ የሚፈልጉ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ERCS 1000040792981 መላክ እንደሚችሉ ተገልጿል።

@tikvahethiopia
2.9K views14:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-12 17:55:25
#Udpate

በጂንካና አካባቢው ከተፈጠረው የፀጥታ ችግር ጋር በተያያዘ በቁጥጥር ስር ከዋሉ ግለሰቦች 22 ሲፈቱ ቀሪዎቹ ላይ ምርመራ መቀጠሉ ተሰምቷል።

ዞኑ ዛሬ በሰጠው መግለጫ የተከሰተው ችግር በቁጥጥር ስር ውሎ ማኅበረሰቡም ወደ ቀደመው የኑሮ ሁኔታ እየተመለሰ ነው ብሏል።

የዞኑ ም/አስተዳዳሪና የሰላም እና ፀጥታ ኃላፊ አቶ ደሞ በዛብህ ፤ ከፀጥታው ችግር ጋር በተያያዘ ተጠርጣሪ ወንጀለኞችን ካሉበት አድኖ በሕግ ጥላ ሥር የማዋል ሥራ እየተሰራ ነው ያሉ ሲሆን ለጊዜው እስካሁን 132 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር ውለዋል፤ ከእነዚህ መካከል በተደረገ የማጥራት ሥራ 22ቱ ዛሬ ተፈተዋል ሲሉ ተናግረዋል።

[NB. ትላንት የደቡብ ፖሊስ ሰጥቶ በነበረው ቃል የተያዙ ተጠርጣሪዎች 133 ናቸው ብሎ ነበር]

አቶ ደሞ የጸጥታ ኃሎች በሰሩት ስራ አብዛኛው አካባቢ አንፃራዊ መረጋጋት መፈጠሩን ገልፀዋል።

በዚህም የቅድመ ማስጠንቀቂያ ባለሙያዎች ለሰብዓዊ ድጋፍ በሚመች መልኩ ተግባራቸውን ለማከናወን ተንቀሳቅሰዋል።

ኃላፊው፤ የፀጥታው ኮማንድ ፖስት ባካሄደው ወቅታዊ ሁኔታ ግምገማ በቶልታና መጸር 145 ቤቶች በእሳት የተቃጠሉ ሲሆን ከዚህ መካከል 1 መስጂድ ይገኝበታል ብለዋል።

አንድ ቀበሌ ያልተጣራ ያለ በመሆኑ ኮማንድ ፖስቱ በቀጣይ አጣርቶ ለሕዝብ ግልጽ ያደርጋል ሲሉ ገልፀዋል።

በጂንካ ዙሪያ 6 ቤቶች መቃጠላቸውን አሳውቀዋል።

በፀጥታ መዋቅሩ የተገመገመና የተለየ የተፈናቀሉ አባወራ 237፤ እማወራ 136 በአጠቃላይ 333 አባወራና እማወራዎች ተፈናቅለው በት/ቤቶችና ፖሊስ ጣቢያዎች ተጠልለው ይገኛሉ።

979 ቤተሰቦች ከቤት-ንብረታቸው የተፈናቀሉ ሲሆን ይህም ለጊዜው በጸጥታ አካላት ተለዩ ናቸው። የቅድመ ማስጠንቀቂያ ሪፖርት ሲመጣ ቁጥሩ ከሚጠበቀው በላይ ሊያሻብቅ እንደሚችል ተገምቷል።

@tikvahethiopia
2.1K views14:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-12 17:55:25
#Russia

የሩሲያው ፕሬዜዳንት ቭላድሚር ፑቲን ሀገራቸውን ሩስያን ለማግለል የሚደረገው ሙከራ አይሳካም ሲሉ ምእራባውያንን አስጠነቀቁ።

ሩስያ በዩክሬን የጀመረችውን " ልዩ ወታራዊ ዘመቻ " ተከትሎ ጠንከር ያሉ ማዕቀቦችን በጣሉባት ምእራባውያን እና አሜሪካ ላይ እምነት እንደማይኖራት ገልጻለች፡፡

ፕሬዜዳንት ፑቲን ፥ " በሶቬት ህብረት ጊዜ ጠቅላላ ማእቀብ ተጥሎ ነበር፤ ሙሉ በሙሉ ተገልላም ነበር፤ ነገርግን ሶቬት አሁንም በስፔስ ቀዳሚ ነች " ሲሉ ተደምጠዋል።

ፕሬዝደንቱ የመገለል ፍላጎት እንደሌላቸው እና በዚህ ዘመናዊ አለም ማግለል እንደማይቻል ተናግረዋል፡፡

በቀዝቃዛው ጦርነት ወቅት ሩሲያ በዩሪ ጋጋሪ አማካኝነት ወደ ስፔስ ያደረገችው በረራ እና በፈረንጆቹ 1957 የስፑትኒክ አንደኛ ወደ ስፔስ መብረር አሜሪካን አስደንግጦ ነበር፡፡ በወቅቱ አሜሪካ ከሩሲያ ጋር ለመወዳደር ስትል ናሳን አቋቁማ ነበር፡፡

ፕሬዜዳንት ፑቲን በዩክሬን " ወታደራዊ ዘመቻ " ለማድረግ የተገደዱት፤ አሜሪካ ዩክሬንን እና ኔቶን በመጠቀም ለማስፈራራት ስለሞከረች እና ይህንም መከላከል ሲለሚገባ ነው ብለዋል፡፡

ፑቲን ሩሲያ በዩክሬን ሁሉንም የምትፈልገውን አላማ ታሳካለች ብለዋል፡፡

ምንጭ፦ አል ዓይን ኒውስ

@tikvahethiopia
1.8K views14:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ