2023-01-20 20:50:49
ኢየሱስ አልሞተም-አልተነሳምም!
****
(ከወንድወሰን እሸቴ)
በአዲስ ኪዳን ከተፃፉት አራቱ ወንጌሎች ውስጥ በጣም ታማኙ የዮሃንስ ወንጌል ነው ምክንያቱም ዮሃንስ እስከ ቀራኒዮ ድረስ ከኢየሱስ ጋር ሳይለይ አብሮት ሰለነበር
ኢየሱስ አጥብቆ ስለሚወደውም ቅርቡ ስለሆነም ጭምር ነው የዮሀንስ ወንጌልን ከሌሎቹ ተለይቶ እንዲታመን ያደረገው (እኔ በግሌ ግን የዮሀንስ ወንጌልን የፃፈው ዮሀንስ ሳይሆን ሌላ ሰው እንደሆነ ባምንም)
ለዚህም ነው የዮሃንስ ወንጌል ፀሃፊ <<ያየነውን እንመሰክራለን-ምስክርነታችንም እውነት ነው>> የሚለው፡፡ይህን ወንጌልም ከሌሎች ወንጌሎች ለየት የሚያደርገው በሌሎች 3ቱ ወንጌሎች ያልተፃፉት "የቃና ዘ-ገሊላ ተአምር"-"የአላዛር-ከሞት የመነሳት" ድርጊት ያለው እዚሁ ወንጌል ላይ ብቻ ሲሆን እዚሁ ወንጌል ላይ የተፃፈውን ነገር መመርመር ከሌሎች ወንጌሎች በተለየ "የትንሳኤውን ምስጢር" ለማወቅ ይረዳል፡፡
በዚህም መሰረት "ትንሳኤ አለ ወይስ የለም?" "ኢየሱስ ሞቷል-አልሞተም?" የሚለውን ለማረጋገጥም በጣም ይጠቅማል ብለው ሰዎቹ ያምናሉ፡፡
በሮማዊያን አገዛዝ ዘመን አጥፊዎችን እና ህግ የጣሱትን "በተመሳቀለ" እንጨት ላይ 'ሰቅሎ' መቅጣት የተለመደ የሰርክ ድርጊት እንደሆነ በኢየሱስ ዘመን ከ37-100 ዓ.ም ግድም የኖረው አይሁዳዊው የታሪክ ፀሃፊ ፍላቪየስ ጆሲፈስ "Antiquity of the Jews" በተባለ መፅሃፉ ላይ ገልፇል፡፡
በተጨማሪም የተሰቀሉት ሰዎች የሚሞቱት ከተሰቀሉ 24 ሰአታት በሗላ እንደሆነ ብዙዎቹም ከዛ በፊት እንደማይሞቱ የአይን እማኝነቱን ሰጥቶ በዚሁ መፅሐፍ ላይ ፅፏል፡፡
ከዚህ አንፃር ኢየሱስ መስቀል ላይ የቆየው ከ6-9 ሰአት ድረስ ለ3 ሰአት ብቻ ነው-ምክንያቱም በአይሁድ እምነት አርብ ቀን 'የመዘጋጀት'ቀን ሲሆን በነጋታው ቅዳሜ ሰንበት ነው
ሰንበትም አርብ ከምሽቱ 12 ሰአት ጀምሮ ስለሚገባ በሰንበትም ምንም መስራት ስለማይቻል በዚህ ምክንያት ነው ኢየሱስን ቶሎ ከተሰቀለበት አውር ደው ወደ መቃብር ቦታ የወሰዱት፡፡
ማርቆስ ወንጌል ምእራፍ 15:44 እንደሚነግረን ለጴንጤናዊው ጲላጦስ የመቶ አለቃው መጥቶ
"ኢየሱስ እንደሞተ" ሲነግረው እና ሐብታሙ የሸንጎ አማካሪ የአርማቲያው ዮሴፍ-"ኢየሱስ እንደሞተ በቶሎ ሰንበት ሳይገባ ወስዶ እንዲቀብረው" ሲለምነው ጲላጦስም በመገረም <አሁኑኑ እንዴት ሞተ?> ብሎ ተደነቀ ይላል፦
ምክንያቱም መስቀል ላይ የተሰቀለ ሰው ስቃይ ቢበዛበትም የደም ዝውውሩ ቆሞ ሊሞት የሚችለው ከ24 ሰአታት በሗላ እንደሆነ ጠንቅቆ የሚያውቀው ጲላጦስ "የመሲሁ" በ3 ሰአታት ውስጥ "መሞት" ገረመውም ግራ አጋባውም፡፡
ወንጌሉ ግን ከኢየሱስ ግራና ቀኝ ተሰቅለው የነበሩት ሁለት ሰዎች እንዳልሞቱ በዮሃንስ ወንጌል 19፡31-35 ላይ ይነግረናል፡፡
በነሱ እምነት ያልሞተ ሰው "ጭኑ" ይሰበራል-የሞተ ግን "ጭኑ" አይሰበርም የሁለቱን ወንበዴዎች ጭን ሲሰብሩ፦ የኢየሱስን ግን አልሰበሩም-ለምን? "እሱ እንደሞተ ሆኖ ነበርና" ነው፡፡
ደግሞ በጣም የሚገርመውና ሳይንስም ያረጋገጠው እውነታ የሞተ ሰው "የደም ዝውውሩ ወዲያው ስለሚቆም" በየትኛውም ሁኔታ ቢመታ-ቢወጋ ደም ሊወጣውም ሆነ ሊፈሰው አይችልም፡፡
ኢየሱስ ግን የሮማው ወታደር በጦር ሲወጋው "ደም" እንደፈሰሰው ወንጌሉ አስረግጦ ይነግረናል፡፡
ከባዱ ምስጢር ግን ያለው ከዛ በፊት የተከናወኑት ረቂቅ ሒደቶች ላይ እንደሆነ አፍ አውጥተው የሚነግሩን ምልክቶች አሉ፡፡
መፅሃፍ ቅዱስ ለምን እንደሆነ በማይታወቅ ስውር ሰዋዊ ሴራ እና ስልታዊ በሆነ ሁኔታ እውቅና ሰጥቶ ባይገልፃቸውም በዛን ወቅት ከሌሎች የአይሁድ ማህበረሰቦች ራሳቸውን ለይተው በምናኔ መሰል ህይወት የሚኖሩ ኑሯቸውን በሙት ባህር አካባቢ ያደረጉ "ኤሲንስ" ተብለው የሚታወቁ አይሁዳዊያን ነበሩ፡፡
እነኚህ ማህበረሰቦች በጋራ የሚኖሩ-የግል ሐብት የሌላቸው-የእንሰሳ ስጋ የማይበሉ?-ጋብቻ የማይፈቅዱ-መሲሁ በተአምር ከኛ ይወለዳል ብለው የሚያምኑ የሙሴ ህግን ቶራውን-ታልሙዱን ጠንቅቀው የሚያውቁ-በባህላዊም ሆነ በዘመኑ በነበረው የህክምና ጥበብ የረቀቁ ሲሆን ኢየሱስም የነሱ አባል ሲሆን፦
በኤሲንሶች እምነት መሰረትም አንድ ሰው በቅቶ ካህን ሆኖ አደባባይ ወጥቶ ማስተማር የሚጀምረው በ30 አመቱ ነው በዚህም መሰረት ጉምቱው ኤሲናዊው የሆነው ዮሃንስ መጥምቁ ኢየሱስን አጥምቆ እና ክህነት አልብሶ ወደ አደባባይ እንደላከው ምስጢራዊው የኤሲንሶች ታሪክ ያሳብቅልናል፡፡
ኢየሱስም ከ12-30 አመቱ ለ18 አመታት ያህል ከኤሲንሶች በቀሰመው ትምርት-ጥበብ እና ተአምር ከፊል እስራኤልን እንደማረከ ይታወቃል፡፡
በዚሁም መሰረት ኢየሱስ ልጁን ከሞት ያዳነለት ሮሜዊው መቶ አለቃ የአርማቲያው ዮሴፍ ራሱ ጲላጦስ በኢየሱስ አስተምህሮት የተማረኩ የኤሲንሶች ደጋፊና አባል ስለነበሩ ኢየሱስ መስቀል ላይ እያለ "አደንዝዞ ትንፋሽን ወደ ውስጥ አስውጦ የሞተ የሚያስመስል ተመስጦ ውስጥ የሚከት "ባህላዊ መድሃኒት" ቀምመው ሰጡት፤ ወታደሮች መጥተው ሲያዩትም ከዛ በፊት ባልተለመደ ሁኔታ ሞቷል-በጦር ሲወጉትም ደም ፈሰሰው የሞተ ሰው ደግሞ ደም አይፈሰውም እነኚህ ሁኔታዎች ደግሞ አለመሞቱን ቁልጭ አድርጎ ያሳያል፡፡
ከዛም በሗላ ኤሲናዊው የአርማቲያው ዮሴፍ የኢየሱስን ስጋ ሊቀብረው ወሰደው በመቃብሩም ቦታ "አትክልት" ነበረው ይሄ እንግዲህ አጋጣሚ ሳይሆን ሆን ተብሎ የተደረገ ነገር ነው፡፡
በህክምና ጥበብ የተካኑት ኤሲናዊያኖቹ ዮሴፍና ኒቆዲሞስ- መቃብሩ ቦታ ከነበሩት እፅዋቶች-መዳኒት ቀምመው በግርፋያ የተጎዳውን የኢየሱስን ገላ ሲያክሙት አደሩ፡፡
በነጋታውም ኢየሱስን በጣም የምትወደው ማሪያም መግደላዊት ወደ መቃብሩ ስትመጣ ሁለት ሰዎች አየች መልአክት ያየች መስሏትም ደነገጠች በድንጋጤም "መልአክት" የመሰሏት ሁለቱ ሰዎች ኢየሱስ በደረሰበት ግርፋት ምክንያት የተጎዳ ሰውነቱን እና ቁስሉን ሲያክሙለት ያደሩት ዮሴፍና ኒቆዲሞስ እንጂ ከሰማይ የመጡ መላእክት አልነበሩም፡፡
ወደ ሗላ ዞር ስትልም ኢየሱስን አየችው "ረቡኒ ብላ" ስትጠጋውም "አትንኪኝ" አላት እንደዛ ያላትም የታከመው ቁስሉ በደንብ ስላልዳነለት እና ስላልጠገገለት ነበር "አትንኪኝ" ያላት፡፡
ስለዚህ "ሳይሞቱ ትንሳኤ የለም!" ይሉናል ሁለቱ ጁርመናዊያን ደራሲዎች ሆልገር ክሬስተንና እና ኤልማር ግራበር "The Jesus conspiracy" በተባለ እ.ኤ.አ በ1994 ዓም በተፃፈ መፅሃፋቸው፡፡
**እንደ መውጪያ*
ኢየሱስ ካልሞተ የት ሔደ??
***
እንግዲህ ኢየሱስ ካልሞተና ሞትን በኤሲንሶች ትብብር ካመለጠ በሗላ የት ሄደ? ለሚለው ጥያቄ መልሱ፦
<< ኢየሱስ ከቀራኒዮ አስቸጋሪ ፈተና የህይወት እና የሞት ትንቅንቅ በሗላ ከ33 አመቱ እስከ 112 አመቱ ድረስ በሕንድ ካሽሚር ውስጥ በደስታና በተድላ በክብር ሲያስተምር ኖሮ በ112 አመቱ እንደሞተ እና የቀበር ስነስረአቱም "ስሪናጋል" በተባለ ቦታ "ሮዝ-ባል" መቅደስ ውስጥ ተፈፅሟል ይለናል"
ጀርመናዊው ሰውዬ ሆልገር ክሪስተን እ.ኤ.አ በ1983 ዓ.ም በፃፈው "Jesus lived in India" በተባለው አነጋጋሪ መፅሃፋ፡፡(ዮሃንስ ወ19:28-48,2:1-11,11:42...ማቴዎስ27:57-58
ማቴ 9:18-25)
22 viewsE@ዮ? , edited 17:50