Get Mystery Box with random crypto!

✥መ/ር ምህረተአብ አሰፋ ፔጅ✣

የቴሌግራም ቻናል አርማ tewahido_ortho — ✥መ/ር ምህረተአብ አሰፋ ፔጅ✣
የቴሌግራም ቻናል አርማ tewahido_ortho — ✥መ/ር ምህረተአብ አሰፋ ፔጅ✣
የሰርጥ አድራሻ: @tewahido_ortho
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.32K
የሰርጥ መግለጫ

ውድ የቻይናላችን ተከታዮች በሙሉ የምለቀቀውን ሸር እያደረጋችሁ ለወዳጅ በማድረስ የድርሻውን ይወጡ #የማንቂያ_ደውል በቴሌግራም እስኪ ጀምር።
#እግዚአብሔር_እንድ_ይላል
በመንገደ ላይ ቁሙ ተመልከቱም
#የቀደመችውንም_መንገድ_ጠይቁ
#መልካምቱ_መንገድ_ወዴት_እንደ_ሆነች_እወቁ
ለነፍሳችሁ ዕረፍት ታገኛላችሁ
#እነርሱ_ግን_አንሄድባትም_አሉ።
✥ት/ኤር 6፤16
⏩በየ እለቱ ሙሉ ትምህርት ያገኙበታል

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-08-25 21:53:48 በዓለ ደብረ ታቦር እና ቡሄ

ጌታችን ምሥጢረ መለኮቱን ለገለጠበት ለበዓለ ደብረ ታቦር እንኳን በሰላም አደረሰን!

ጌታችን አምላካችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በደብረ ታቦር ብርሃነ መለኮቱን፣ ክብረ መንግሥቱን መግለጡን በማሰብ በየዓመቱ ነሐሴ ፲፫ ቀን በዓሉ በድምቀት ይከበራል፡፡ ይህ በዓል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምእመናን ዘንድ ‹ቡሄ› በመባል ይታወቃል፡፡ ቡሄ ማለት ‹መላጣ፣ ገላጣ› ማለት ነው፡፡ በአገራችን ክረምቱ፣ ጭጋጉ፣ ደመናው ተወግዶ የብርሃን ወገግታ የሚታይበት በዚሁ በዓል አካባቢ ስለ ኾነ በዓሉ ‹ቡሄ› ተብሎ ይጠራል፡፡ በዓለ ደብረ ታቦር ጌታችን ምሥጢረ መለኮቱን የገለጠበት፤ ብርሃን የታየበትና ድምፀ መለኮቱ የተሰማበ  ዕለት ስለ ኾነ ‹የብርሃን› ወይም ‹የቡሄ› በዓል ይባላል፡፡

ቡሄ ሲመጣ የክረምቱ ጨለማነት አልፎ ወደ ብርሃን፣ ወደ ጥቢ የሚያመራበት፤ ወደ መፀው የሚገባበት፤ ወገግታ የሚታይበት፤ ሰማይ ከጭጋጋማነት ወደ ብሩህነት የሚሸጋገርበት ወቅት በመኾኑ ከቡሄ በኋላ የጠነከረ ክረምት አይኖርም፡፡ ‹‹ቡሄ ከዋለ የለም ክረምት፤ ዶሮ ከጮኸ የለም ሌሊት›› እንዲሉ፡፡ በአንዳንድ የአገራችን አካባቢዎች የቡሄ ዕለት ማታ ምእመናን ችቦ ያበራሉ፡፡ ይህም በደብረ ታቦር ለታየው ብርሃነ መለኮት ምሳሌ ነው፡፡ ሕፃናቱ ይህ በዓል ከመድረሱ በፊት ቀደም ብለው ጅራፍ ሲገምዱና ሲያጮኹ (ሲያኖጉ) ይሰነብታሉ፡፡ እናቶችም ለዚህ በዓል የሚኾን ዳቦ ለመጋገር ስንዴያቸውን ሲያጥቡ፣ ሲፈትጉ ይሰነብታሉ፡፡ በበዓሉ ዋዜማ (ነሐሴ ፲፪ ቀን) ሕፃናት በየቤቱ እየዞሩ ‹‹ቡሄ ና በሉ፤ ቡሄ በሉ፡፡ ቡሄ መጣ፤ ያ መላጣ፤ ቅቤ ቀቡት እንዳይነጣ …›› እያሉ ይጫወታሉ፡፡ በዚህ ጊዜ እናቶች ካዘጋጁት ዳቦ እያነሡ ይሰጧቸዋል፡፡ ሕፃናቱ ‹ቡሄ› የሚሉትም ዳቦውን ነው፡፡

ጌታችን ብርሃነ መለኮቱን በገለጠበት ዕለት እረኞች ከብርሃኑ የተነሣ እየተገረሙና እየተደነቁ ወደ ቤት አልተመለሱም ነበር፡፡ የልጆቹን መዘግየት ያዩ ወላጆች ችቦ አብርተውና ዳቦ ይዘው ፍለጋ ወጥተዋል፡፡ ‹ቡሄ› ለሚሉ ልጆች ሙልሙል ዳቦ የሚሰጠውና በበዓሉ ችቦ የሚበራውም ከዚህ ታሪክ በመነሣት ነው፡፡ ለክርስትና ልጅ፣ ለአማች፣ ለምራት፣ ለዘመድ አዝማድ ዅሉ የቡሄ ዳቦ ይሰጣል፡፡ ልጆችም ዳቧቸውን እየገመጡ ጅራፍ ሲገርፉ ይውላሉ፡፡ የጅራፉ መጮኽ የድምፀ መለኮት ምሳሌ ሲኾን፣ ጅራፉ ሲጮኽ ማስደንገጡም ነቢያትና ሐዋርያት በድምፀ መለኮት መደንገጣቸውንና መውደቃቸውን ያስታውሳል፡፡

መምህረ ሐዋርያት ኢየሱስ ክርስቶስ ሦስቱን ተማሪዎቹን ጴጥሮስን፣ ያዕቆብንና ዮሐንስን ይዞ በደብረ ታቦር ምሥጢር መግለጡን በማስታዎስ የአብነት ተማሪዎች ከመምህራቸው ጋር በመኾን በዓለ ደብረ ታቦርን (ቡሄን) ያከብራሉ፤ ስሙን ይጠራሉ፡፡ የአብነት ተማሪዎች ‹‹ስለ ደብረ ታቦር›› እያሉ እኽል ከምእመናን በመለመንና ገንዘብ በማዋጣት ጠላውን ጠምቀው፣ ዳቦውን ጋግረው፣ ቆሎውን ቆልተው ለደብረ ታቦር ዕለት ሊያስቀድሱ የመጡትን ምእመናን በመጋበዝና እርስበርስ በመገባበዝ፣ እንደዚሁም ቅኔ በማበርከት በዓለ ደብረ ታቦርን በታላቅ ድምቀት ያከብራሉ፡፡ ይህም እስከ አሁን ድረስ በአብነት ትምህርት ቤቶች የሚሠራበት ነባር ትውፊት ነው፡፡

ነገር ግን በአንድ አካባቢዎች በተለይ በከተማ ዙሪያ በዓለ ደብረ ታቦር (ቡሄ) ሃይማኖታዊ ትውፊቱን የለቀቀ ይመስላል፡፡ ለዚህም ልጆች የሚጫወቱበት መዝሙር ግጥሙና ዜማው ዓለማዊ መልእክት የሚበዛበት መኾኑ፤ በወቅቱ ችቦ ከማብራት ይልቅ ርችት መተኮሱና በየመጠጥ ቤቱ እየሰከሩ መጮኹ፤ ወዘተ. የበዓሉን መንፈሳዊ ትውፊት ከሚያደበዝዙ ተግባራት መካከል የሚጠቀሱ ናቸው፡፡ ከዚሁ ዅሉ ጋርም በዚህ በዓል ገንዘብ ለመሰብሰብ ብቻ የሚሽቀዳደሙ ነገር ግን የበዓሉን ታሪካዊ አመጣጥ የማያዉቁ ልጆችም ጥቂቶች አይደሉም፡፡

ስለዚህ ወላጆች ለልጆቻቸው የበዓለ ደብረ ታቦርን መንፈሳዊነት፣ የመዝሙሮቹን ያሬዳዊነትና አከባበሩን ከቤተ ክርስቲያን መምህራን በመጠየቅ ማስተማር፤ ልጆችም ከወላጆች ወይም ከመምህራን በመጠየቅ የበዓሉን አከባበር መረዳትና የዚህን በዓል መንፈሳዊ ትውፊት ሳይበረዝ ለትውልድ ማስተላለፍ ይገባቸዋል፡፡ ‹‹ድምፅህን ሰማና በብሩህ ደመና፤ የቡሄው ብርሃን ለእኛ በራልን …›› የሚለውንና ይህን የሚመስሉ መንፈሳውያን መዝሙራትን እየዘመሩ በየቤቱ በመዘዋወር የሚያገኙትን ዳቦና ገንዘብ ለነዳያንና ለቤተ ክርስቲያን የሚሰጡ ልጆችንም ማበረታታትና አርአያነታቸውን መከተል ይኖርብናል፡፡

መልካም በዓል ይኹንልን!

ወስብሐት ለእግዚአብሔር

ምንጭ፡-
መጽሐፈ ታሪክ ወግስ፣ መ/ር አፈወርቅ ተክሌ፤ ፳፻፭ ዓ.ም፣ ገጽ ፫፻፲፭-፫፻፲፯፡፡
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ፣ ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ፤ ፳፻፯ ዓ.ም፣ ገጽ ፻፲፩፡፡


ቻይናል ይቀላቀሉ ሸር ያድርጉ አብረውን ይሁኑ


https://telegram.me/tewahido_ortho
299 views18:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-12 00:20:05
https://t.me/tewahido_ortho
1.5K viewsedited  21:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-16 23:03:40 ➤ (የሐዋ 4፡12)
► “እነሆ፥ አምላካችሁ በበቀል በእግዚአብሔርም ብድራት ይመጣልና፥ መጥቶም ያድናችኋልና በርቱ፥ አትፍሩ በሉአቸው”
➤(ኢሳ 35፡4) ╬ “ጌታ ኢየሱስ ከሥልጣኑ መላእክት ጋር ከሰማይ በእሳት ነበልባል ሲገለጥ፥ መከራን ለሚያሳዩአችሁ መከራን፥ መከራንም ለምትቀበሉ ከእኛ ጋር ዕረፍትን ብድራት አድርጎ እንዲመልስ በእግዚአብሔር ፊት በእርግጥ ጽድቅ ነውና እግዚአብሔርን የማያውቁትን ለጌታችንም ለኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌል የማይታዘዙትን ይበቀላል”
➤ (2ተሰ 1፡7-8)
► “የአዋጅ ነጋሪ ቃል። የእግዚአብሔርን መንገድ በምድረ በዳ ጥረጉ

#ይቀጥላል
ለተዋህዶ ልጅች ሸር ያድርጉ

ወስብሐት ለእግዚአብሔር

https://t.me/timhirte_tewahido
2.0K views20:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-16 23:00:29 #አልተሳሳትንም_ኢየሱስ_ክርስቶስ_እግዚአብሔር_ነው .......ብዙዎች በዘመናችን #የመጽሐፍ_ቅዱስን ትምህርት ባለመረዳትና “ #እኔና_አብ_አንድ_ነን” ያለውን የአምላካችን የኢየሱስ ክርስቶስን የባሕርይ አምላክነትን፣ ፈጣሪነት፣ ፍጹም ተዋሕዶውን ፈራጅነቱን በመካድ #ሎቱ_ስብሐት ከአብ አሳንሰው ርሱን #ለማኝ አብን #ተለማኝ ያደርጋሉ፤ ቅድስት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናችን ከበፊት ጀምሮ እስካሁን ከመናፍቃን የሚደርስባት ፈተና ለምን ኢየሱስ ክርስቶስን የባሕርይ አምላክ ነው? ለምን ከአባቱ ጋር የተካከለ ፈራጅ ነው? ብለሽ ታስተምሪያለሽ የሚል ነው፤
ይህም ዐዲስ አይደለም የባሕርይ አምላክነቱን፣ ተዋሕዶውን፣ ፈራጅነቱን ከካዱት ውስጥ ከቀድሞዎቹ እነ ጳውሎስ ሳምሳጢ፣ አርዮስ፣ ንስጥሮስ …. በ16ኛው መቶ ክ.ዘመን ወዲህ በየዘመናቱ የሚነሱ የእምነት ድርጅቶች ወ.ዘ.ተ ይገኛሉ፤ የእነዚኽን አስተምህሮ በምንማርበት የነገረ መለኮት ኮሌጅ ውስጥ ከደቀ መዛሙርት ጋር በክፍል ውይይት ጊዜ በጥልቀት የምዳስሰው ቢኾንም፤ ለ ፌስ ቡክ (face book) ጓደኞቼ ግን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ የምታስተምረውን በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ የተጻፈውን አስተምህሮ ጥቂቱን ከዚኽ በታች አስፍሬዋለኊ፡- ይኸውም በብሉይ ኪዳን የተጠቀሰው እግዚአብሔር ከሦስቱ አካል አንዱ እግዚአብሔር ወልድ ኢየሱስ ክርስቶስ ስለመኾኑ የተጻፈውን የብሉይ ኪዳንና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍትን እውነት በማንበብ አረጋግጡ፡-

ሀ) ኢየሱስ ክርስቶስ በእውነት እግዚአብሔር ነው እንላለን፡፡
►“በመጀመሪያ እግዚአብሔር ሰማይንና ምድርን ፈጠረ”
➤(ዘፍ 1፡1) ╬ “ጌታ ሆይ፥ አንተ ከጥንት ምድርን መሠረትህ ሰማዮችም የእጆችህ ሥራ ናቸው
➤” (ዕብ 1፡10)
►“እግዚአብሔርም ሙሴን፦ «ያለና የሚኖር» እኔ ነኝ አለው እንዲህ ለእስራኤል ልጆች። «ያለና የሚኖር» ወደ እናንተ ላከኝ ትላለህ አለው”
➤ (ዘፀ 3፡14) ╬ “ያለውና የነበረው የሚመጣውም ሁሉንም የሚገዛ ጌታ አምላክ። አልፋና ዖሜጋ እኔ ነኝ ይላል”
➤ (ራእ 1፡8)
►“ለአንተ ከአንተም በኋላ ለልጆችህ መልካም ይሆን ዘንድ፥ አምላክህም እግዚአብሔር ለዘላለም በሚሰጥህ ምድር ዕድሜህ ይረዝም ዘንድ፥ እኔ ዛሬ የማዝዝህን ሥርዓቱንና ትእዛዙን ጠብቅ”
➤ (ዘዳ 4፡40) ╬ “እርስ በርሳችሁ እንድትዋደዱ ይህን አዛችኋለሁ”
➤ (ዮሐ 15፡17)
►“አምላካችንን እግዚአብሔርን እናመልካለን፥ ድምፁንም እንሰማለን”
➤(ኢያ 24፡24) ╬ “ከጌታ የርስትን ብድራት እንድትቀበሉ ታውቃላችሁና የምታገለግሉት ጌታ ክርስቶስ ነውና”
➤ (ቆላ 3፡24)
► “እግዚአብሔርን ብትፈሩ ብታመልኩትም፥ ቃሉንም ብትሰሙ፥ በእግዚአብሔርም ትእዛዝ ላይ ባታምፁ፥ እናንተና በእናንተ ላይ የነገሠው ንጉሥ አምላካችሁን እግዚአብሔርን ብትከተሉ፥ መልካም ይሆንላችኋል”
➤(1 ሳሙ 12፡14) ╬ “ደግሞም ኢየሱስ፦ እኔ የዓለም ብርሃን ነኝ፤ የሚከተለኝ የሕይወት ብርሃን ይሆንለታል እንጂ በጨለማ አይመላለስም ብሎ ተናገራቸው”
➤(ዮሐ 8፡12)
► “አንተ ብቻ የሰውን ልጆች ሁሉ ልብ ታውቃለህና ልቡን ለምታውቀው ሰው ሁሉ እንደ መንገዱ ሁሉ መጠን ክፈለውና ስጠው”
➤(1ነገ 8፡39) ╬ “ነገር ግን ኢየሱስ ሰዎችን ሁሉ ያውቅ ነበር፤ ስለ ሰውም ማንም ሊመሰክር አያስፈልገውም ነበርና አይተማመናቸውም ነበር፤ ራሱ በሰው ያለውን ያውቅ ነበርና”
➤ (ዮሐ 2፡25፤ 1ቆሮ 4፡5)
► “አንተ ብቻ እግዚአብሔር ነህ ሰማዩንና የሰማያት ሰማይን ሠራዊታቸውንም ሁሉ፥ ምድሩንና በእርስዋ ላይ ያሉትን ሁሉ፥ ባሕሮቹንና በእነርሱ ውስጥ ያለውን ሁሉ፥ ፈጥረሃል፥ ሁሉንም ሕያው አድርገኸዋል የሰማዩም ሠራዊት ለአንተ ይሰግዳሉ”
➤(ነህ 9፡6) ╬ “ደግሞም በኵርን ወደ ዓለም ሲያገባ። የእግዚአብሔር መላእክት ሁሉም ለእርሱ ይስገዱ”
➤(ዕብ 1፡6) ╬ “ይህም በሰማይና በምድር ከምድርም በታች ያሉት ሁሉ በኢየሱስ ስም ይንበረከኩ ዘንድ”
➤ (ፊልጵ 2፡10)
► “ከእግዚአብሔር በቀር አምላክ ማን ነው? ከአምላካችን በቀር አምላክ ማን ነው?”
➤(መዝ 17 (18)፡31 ╬ “እርሱም ልጁ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው እርሱ እውነተኛ አምላክና የዘላለም ሕይወት ነው”
➤ (1ዮሐ 5፡20)
► “እግዚአብሔር እረኛዬ ነው፥ የሚያሳጣኝም የለም”
➤(መዝ 22(23)፡1) ╬ “መልካም እረኛ እኔ ነኝ መልካም እረኛ ነፍሱን ስለ በጎቹ ያኖራል”
➤(ዮሐ 10፡11)
► “እግዚአብሔር ብርሃኔና መድኃኒቴ ነው የሚያስፈራኝ ማን ነው?”
➤(መዝ 26(27)፡1) ╬ “ደግሞም ኢየሱስ፦ እኔ የዓለም ብርሃን ነኝ፤ የሚከተለኝ የሕይወት ብርሃን ይሆንለታል እንጂ በጨለማ አይመላለስም ብሎ ተናገራቸው”
➤(ዮሐ 8፡12)
► “አምላክ በእልልታ፥ እግዚአብሔር በመለከት ድምፅ ዐረገ”
(መዝ 46፡5) ╬ “ሲባርካቸውም ከእነርሱ ተለየ ወደ ሰማይም ዐረገ”
➤ (ሉቃ 24፡51)
► “ከክብሩ ውበት ከጽዮን እግዚአብሔር ግልጥ ሆኖ ይመጣል”
➤(መዝ 49፡2) ╬ “ይህ ከእናንተ ወደ ሰማይ የወጣው ኢየሱስ ወደ ሰማይ ሲሄድ እንዳያችሁት፥ እንዲሁ ይመጣል”
➤(የሐዋ 1፡11)
► “ለስሙም ዘምሩ ለምስጋናውም ክብርን ስጡ”
➤ (መዝ 65፡2)
“መላስም ሁሉ ለእግዚአብሔር አብ ክብር ኢየሱስ ክርስቶስ ጌታ እንደ ሆነ ይመሰክር ዘንድ ነው”
➤(ፊልጵ 2፡11)

► “እግዚአብሔርም ከእንቅልፍ እንደሚነቃ ተነሣ የወይን ስካር እንደ ተወው እንደ ኃያልም ሰው”
➤ (መዝ 77፡65) ╬ “እንደ ተናገረ ተነሥቶአልና በዚህ የለም፤ የተኛበትን ስፍራ ኑና እዩ”
➤(ማቴ 28፡6)

► “ይመጣልና በምድር ላይ ሊፈርድ ይመጣልና እርሱም ዓለምን በጽድቅ አሕዛብንም በቅንነት ይፈርዳል”
➤ (መዝ 95፡13) ╬ “ሰዎች ሁሉ አብን እንደሚያከብሩት ወልድን ያከብሩት ዘንድ ፍርድን ሁሉ ለወልድ ሰጠው እንጂ አብ በአንድ ሰው ስንኳ አይፈርድም”
➤(ዮሐ 5፡22)

► “በተጨነቁ ጊዜ ወደ እግዚአብሔር ጮኹ በመከራቸውም አዳናቸው ከጨለማና ከሞት ጥላ አወጣቸው፥ እስራታቸውንም ሰበረ”
➤(መዝ 106፡13-14) ╬ “በጨለማ የተቀመጠው ሕዝብ ታላቅ ብርሃን አየ፥ በሞት አገርና ጥላ ለተቀመጡትም ብርሃን ወጣላቸው”
➤(ማቴ 4፡16)

► “ከእግዚአብሔር ዘንድ ምሕረት፥ በእርሱም ዘንድ ብዙ ማዳን ነውና እስራኤል በእግዚአብሔር ይታመን”

➤ (መዝ 129፡7) ╬ “ሰዎችን ሁሉ የሚያድን የእግዚአብሔር ጸጋ ተገልጦአልና
➤ (ቲቶ 2፡11)
► “እግዚአብሔር የወደደውን ይገሥጻልና፥ አባት የሚወድደውን ልጁን እንደሚገሥጽ”
➤ (ምሳ 3፡12) ╬ “እኔ የምወዳቸውን ሁሉ እገሥጻቸዋለሁ እቀጣቸውማለሁ፤ እንግዲህ ቅና ንስሐም ግባ”
➤ (ራእ 3፡19)

► “ እነሆ፥ አምላክ መድኃኒቴ ነው ጌታ እግዚአብሔር ኃይሌና ዝማሬዬ ነውና፥ መድኃኒቴም ሆኖአልና በእርሱ ታምኜ አልፈራም ትላለህ”
➤(ኢሳ 12፡2) ╬ “መዳንም በሌላ በማንም የለም፤ እንድንበት ዘንድ የሚገባን ለሰዎች የተሰጠ ስም ከሰማይ በታች ሌላ የለምና”
2.2K views20:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-02 08:45:13 #እንኳን_ለብርሃነ_ዕርገቱ_አደረሰን ✥ ✥ ✥
“ እስከ ቢታንያም አወጣቸው። እጆቹንም አንስቶ ባረካቸው:: ሲባርካቸውም ከእነርሱ ተለየ፡፡ #ወደ_ሰማይም_ዐረገ :: እነርሱም ሰገዱለትና በብዙ ደስታ ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ....”(ሉቃ.፳፬፡፵፰-፶፩ )


ምስባክ፦
ዐርገ እግዚአብሔር በይባቤ፤
ወእግዚእነ በቃለ ቀርን፤
ዘምሩ ለአምላክነ ዘምሩ።

ዕርገት ማለት ወደ ላይ ከፍ ከፍ ማለት ሲሆን የመሬትን የስበት ኃይል የሚያሸንፍ ከፍታ ነው፡፡ ክርስቶስ ወደ ሰማይ ያረገው የመሬት የስበት ኃይል ሳይገድበው ነው፡፡ የክርስቶስ ዕርገት ቀድሞ በትንቢት የተነገረ፤ በሚያምኑት ዘንድ በናፍቆት ሲጠበቅ የቆየ እና በራሱ በጌታችን የተሰበከ ነው፡፡
ጌታችን መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትን ድል አድርጎ ከተነሳ በኋላ ለሰላሳ ዘጠኝ ቀናት ያህል ለሐዋርያቱ በተለያየ ጊዜ እየተገለጠ ለአገልግሎት ሲያዘጋጃቸው እና ስለ እግዚአብሔር መንግሥት ምስጢር እያስተማራቸው ከቆየ በኋላ በ፵ኛው ቀን በሐዋርያቱ ፊት ዐርጎል። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ከምታከብራቸው የጌታችንን ዓበይት በዓላት አንዱ ዕርገት ነው።

ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ በተነሣ በ፵ኛው ቀን ወደ ሰማይ ዐረገ ያረገበትም ቦታ ቢታንያ አጠገብ የሚገኘው ደብረ ዘይት የሚባለው ተራራ ነው። አሥራ አንዱ ሐዋርያትን እዚያ ድረስ ከወሰዳቸው በኋላ ባርኳቸው እያዩት ዐረገ። ደመና ከዓይናቸው ሰውራ ተቀበለችው። በእግዚአብሔርም ቀኝ ተቀመጠ። ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ቀደመ ክብሩ፤ በመለኮታዊ ክብሩ ወደ ሰማይ ዐርጎ በአባቱ ቀኝ ተቀምጧል። ጌታችን ያረገውም በለበሰው ሥጋ በመሆኑ እና ለሁለተኛ ጊዜ ለፍርድ በሚመጣበት ጊዜ ይህን ክብር እኛም እንድናገኝ ምሳሌ ሲሆነን ነው። "በሚመጡ ዘመናትም በክርስቶስ ኢየሱስ ለእኛ ባለው ቸርነት ከሁሉ የሚበልጠውን የጸጋውን ባለ ጠግነት ያሳይ ዘንድ ፥ ከእርሱ ጋር አስነሣን በክርስቶስ ኢየሱስም በሰማያዊ ስፍራ ከእርሱ ጋር አስቀመጠን።" (ኤፌ . ፪፡፮)

ጌታችን መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ ዕርገቱ አስመልክቶ ከተናገራቸው ሦስት ነገሮች ውስጥ፦
✥ የመጀመሪያው፤ "እኔም ከምድር ከፍ ከፍ ያልሁ እንደ ሆነ ሁሉን ወደ እኔ እስባለሁ።" (ዮሐ .፲፪፡፴፪)
✥ ሁለተኛው ደግሞ፤ "ወላጆች እንደ ሌላቸው ልጆች አልተዋችሁም፤ ወደ እናንተ እመጣለሁ።"(ዮሐ.፲፬፡፲፰)
✥ ሶስተኛው፤ "እኔ ግን እውነት እነግራችኋለሁ፤ እኔ እንድሄድ ይሻላችኋል። እኔ ባልሄድ አጽናኙ ወደ እናንተ አይመጣምና፤ እኔ ብሄድ ግን እርሱን እልክላችኋለሁ።" (ዮሐ .፲፮፡፯)

የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ዕርገት ለእኛ ትልቅ ተስፋ ነው ስለዚህም ሐዋርያት ጌታችን ሲያርግ ወደ ሰማይ ትኩር ብለው ይመለከቱት እንደነበር እኛም በታላቅ ተስፋ የጌታን ነገር ልናስብ ይገባል። ነቢዩ ዳንኤል ስለ ጌታችን ዕርገት እና በአብ ቀኝ ስለመቀመጡ እንዲህ ሲል በትንቢት ተናግሮ ነበር፤ "በሌሊት ራእይ አየሁ፤ እነሆም፥ የሰው ልጅ የሚመስል ከሰማይ ደመናት ጋር መጣ በዘመናት ወደ ሸመገለውም ደረሰ፤ ወደ ፊቱም አቀረቡት። ወገኖችና አሕዛብ በልዩ ልዩ ቋንቋም የሚናገሩ ሁሉ ይገዙለት ዘንድ ግዛትና ክብር መንግሥትም ተሰጠው፤ ግዛቱም የማያልፍ የዘላለም ግዛት ነው፥መንግሥቱም የማይጠፋ ነው።" (ዳን.፯፡፲፫ - ፲፬) ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ካረገ በኋላ በአብ ቀኝ ተቀመጠ ስንል ጌታ ከአብ ጋር እኩል ነው ማለታችን ነው።
ከ፬ቱ ወንጌላውያን ውስጥ ይህን የዕርገቱን ታሪክ የመዘገቡት ቅዱስ ማርቆስ እና ቅዱስ ሉቃስ ናቸው።
"ከሳምንቱም በመጀመሪያው ቀን ማልዶ በተነሣ ጊዜ፥ አስቀድሞ ሰባት አጋንንት ላወጣላት ለመግደላዊት ማርያም ታየ።እርስዋ ሄዳ ከእርሱ ጋር ሆነው ለነበሩት ሲያዝኑና ሲያለቅሱ ሳሉ አወራችላቸው፤ እነርሱም ሕያው እንደ ሆነ ለእርስዋም እንደታያት ሲሰሙ አላመኑም። ከዚህም በኋላ ከእነርሱ ለሁለቱ ወደ ባላገር ሲሄዱ በመንገድ በሌላ መልክ ተገለጠ፤ እነርሱም ሄደው ለሌሎቹ አወሩ፤ እነዚያንም ደግሞ አላመኑአቸውም። ኋላም በማዕድ ተቀምጠው ሳሉ ለአሥራ አንዱ ተገለጠ፥ ተነሥቶም ያዩትን ስላላመኑአቸው አለማመናቸውንና የልባቸውን ጥንካሬ ነቀፈ። እንዲህም አላቸው። ወደ ዓለም ሁሉ ሂዱ ወንጌልንም ለፍጥረት ሁሉ ስበኩ። ያመነ የተጠመቀም ይድናል፥ ያላመነ ግን ይፈረድበታል። ያመኑትንም እነዚህ ምልክቶች ይከተሉአቸዋል፤ በስሜ አጋንንትን ያወጣሉ፤ በአዲስ ቋንቋ ይናገራሉ፤ እባቦችን ይይዛሉ፥ የሚገድልም ነገር ቢጠጡ አይጎዳቸውም፤ እጃቸውን በድውዮች ላይ ይጭናሉ እነርሱም ይድናሉ። ጌታ ኢየሱስም ከእነርሱ ጋር ከተናገረ በኋላ ወደ ሰማይ ዐረገ በእግዚአብሔርም ቀኝ ተቀመጠ።" (ማር.፲፮፡፱-፲፱)

"እናንተም ለዚህ ምስክሮች ናችሁ። እነሆም፥ አባቴ የሰጠውን ተስፋ እኔ እልክላችኋለሁ፤ እናንተ ግን ከላይ ኃይል እስክትለብሱ ድረስ በኢየሩሳሌም ከተማ ቆዩ። እስከ ቢታንያም አወጣቸው እጆቹንም አንሥቶ ባረካቸው። ሲባርካቸውም ከእነርሱ ተለየ ወደ ሰማይም ዐረገ።" (ሉቃ.፳፬፡፵፰-፶፩)
ቅዱስ ሉቃስ የሐዋርያት ሥራን ሲጽፍ ስለ ጌታችን መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዕርገት አብራርቶ ጽፎታል። እንዲህ ሲል፦
"ደግሞ አርባ ቀን እየታያቸው ስለ እግዚአብሔርም መንግሥት ነገር እየነገራቸው፥ በብዙ ማስረጃ ከሕማማቱ በኋላ ሕያው ሆኖ ለእነርሱ ራሱን አሳያቸው። ከእነርሱም ጋር አብሮ ሳለ ከኢየሩሳሌም እንዳይወጡ አዘዛቸው፥ ነገር ግን። ከእኔ የሰማችሁትን አብ የሰጠውን የተስፋ ቃል ጠብቁ፤ ዮሐንስ በውኃ አጥምቆ ነበርና፥ እናንተ ግን ከጥቂት ቀን በኃላ በመንፈስ ቅዱስ ትጠመቃላችሁ አለ። እነርሱም በተሰበሰቡ ጊዜ። ጌታ ሆይ፥ በዚህ ወራት ለእስራኤል መንግሥትን ትመልሳለህን? ብለውጠየቁት። እርሱም አብ በገዛ ሥልጣኑ ያደረገውን ወራትንና ዘመናትን ታውቁ ዘንድ ለእናንተ አልተሰጣችሁም፤ ነገር ግን መንፈስ ቅዱስ በእናንተ ላይ በወረደ ጊዜ ኃይልን ትቀበላላችሁ፥ በኢየሩሳሌምም በይሁዳም ሁሉ በሰማርያም እስከ ምድር ዳርም ድረስ ምስክሮቼ ትሆናላችሁ አለ። ይህንም ከተናገረ በኋላ እነርሱ እያዩት ከፍ ከፍ አለ፤ ደመናም ከዓይናቸው ሰውራ ተቀበለችው። እርሱም ሲሄድ ወደ ሰማይ ትኵር ብለው ሲመለከቱ ሳሉ፥ እነሆ፥ ነጫጭ ልብስ የለበሱ ሁለት ሰዎች በአጠገባቸው ቆሙ፤ ደግሞም። የገሊላ ሰዎች ሆይ፥ ወደ ስማይ እየተመለከታችሁ ስለ ምን ቆማችኋል? ይህ ከእናንተ ወደ ሰማይ የወጣው ኢየሱስ ወደ ሰማይ ሲሄድ እንዳያችሁት፥ እንዲሁ ይመጣል አሉአቸው።" (ሐዋ.፩፡፫-፲፩)

ክርስቲያኖች በሰማያት ስፍራ ከጌታችን ከመድሃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር አብረው እንደሚቀመጡ የእርሱ ዕርገት ያረጋግጥልናል። ቅዱስ ጳውሎስም ስለ ጌታችን እርገት እንዲህ ሲል ይመክረናል፤ " እንግዲህ ከክርስቶስ ጋር ከተነሣችሁ፥ ክርስቶስ በእግዚአብሔር ቀኝ ተቀምጦ ባለበት በላይ ያለውን እሹ። በላይ ያለውን አስቡ እንጂ በምድር ያለውን አይደለም። ሞታችኋልና፥ ሕይወታችሁም በእግዚአብሔር ከክርስቶስ ጋር ተሰውሮአልና። ሕይወታችሁ የሆነ ክርስቶስ በሚገለጥበትጊዜ፥ በዚያን ጊዜ እናንተ ደግሞ ከእርሱ ጋር በክብር ትገለጣላችሁ።" (ቆላ. ፫፡፩-፬)



ወስብሐት ለእግዚአብሔር


https://t.me/tewahido_ortho
2.0K views05:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-01 23:44:52

1.4K views20:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-25 22:04:44 "አቤቱ ጌታዬ ንጉሤ ሆይ የራሴን ጥፋት አስመልክተኝ እንጂ በወንድሜ ላይ እንድፈርድ አታድርገኝ፡፡"

#ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ
1.8K views19:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-05 22:08:21 #ትምህርተ_ንስሐ_በአቡነ ሺኖዳ)
@tewahido_ortho

ክፍል

ንስሐ ምንድነው

➾ ንስሐ ነስሐ ከሚል የግዕዝ ግስ የወጣ ቃል ነው። የቃሉ ፍቺ ሐዘን ፣ ፀፀት ፣ ቁጭት ፣ ማለት ነው ። አንድ ሰው ንስሐ ገባ ሲባልም አዘነ ፣ ተፀፀተ ፣ ክፉ አመሉን ተወ ማለት ነው ። ➾ንስሐ ማለት ደግሞ አንድ ሰው በሰራው ጥፋት ባደረገው ስህተት ፣በፈፀመው ኀጢአት ማዘኑና መቆርቆሩ ዳግመኛም ያንን የመሰለ ኀጢአት ላለማድረግ የሚወስነው ውሳኔ ነው ። በአጠቃላይ ንስሐ ከፍ ብሎ የተገለጠውን ትርጉም ሲኖረው በሰዎች ህይወት ውስጥ ደግሞ የሚከተሉትን ፍችዎች ይዞ እናገኘዋለን።
➥ሀ➝ ንስሀ ወደ እግዚአብሔር መመለስ ነው። ➠ኀጢአት ከእግዚአብሔር መለየት ነውና። እግዚአብሔር አምላክም በነብያት አድሮ ህዝቡ እንዲመለሱ አዟል። "ከአባቶቻችሁ ዘመን ጀምሮ ከሥርዓቴ ፈቀቅ ብላችኋል። እርሷንም አልጠበቃችሁም። ወደ እኔ ተመለሱ እኔም ወደ እናንተ እመለሳለው። " (ሚል 3:6) በማለት ጥሪውን አስተላልፏል። በመፅሐፈ ምሳሌም "ኀጢአቱን የሚሰውር አይለማም ፣ የሚናዘዝባትና የሚተዋት ግን ምሕረትን ያገኛል" በማለት ተፅፏል። (ምሳ 28:13) በሉቃስ ወንጌል የምናገኘው አባካኙ ልጅ ኃጢአቱ በመረረውና በተፀፀተ ጊዜ ወደ ልቡ ሲመለስ ወደአባቱ ለመምጣት ወሰነ አባቱም በሐሴት ተቀበለው ። (ሉቃ 15:18-20) እውነተኛ ንስሀም ሰዎች በበደልና ኃጢአት ምክንያት ወደ አጡት ሥፍራ ለመመለስ የሚኖራቸው ናፍቆትና ውሳኔ ነው።
➥ለ➝ ንስሀ ከኀጢአት እንቅልፍ መንቃት ነው። ኃጢአት በመንፈሳዊ ሕይወት ማንቀላፋት ነውና ። ኀጢአተኛ ያለበትን ስፍራ የወደቀበትን ጉድጓድ አያውቀውምና በንስሐ መቀስቀስ ያስፈልገዋል ። ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ "ከእንቅልፍ የምትነሱበት ሰዓት አሁን እንደ ደረሰ ዘመኑን እወቁ " በማለት የተናገረው ።
➥ሐ➝ ንስሐ ወደ መንፈሳዊ ሕይወት መመለስ ነው ። ኃጢአት የነፍስ ሞት ነውና ። ቅዱስ ጳውሎስ "በኃጢአታችን ሞተን ሳለን በክርስቶስ አዳነን " ብሏል ። (ኤፌ2:5) ዳግመኛም "አንተ የምትተኛ ንቃ ከሙታንም ተነሳ ክርስቶስም ያበራልሀል " ሲል ተናግሯል ። (ኤፌ 5:10) ቅዱስ ዮሐንስም "እኛ ...ከሞት ወደ ሕይወት እንደተሻገርን እናውቃለን " ብሏል ። (1ኛ ዮሐ 3:14) ቅዱስ ያዕቆብ ደግሞ "ኃጢአተኛን ከተሳሳተበት መንገድ የሚመልሰው ነፍሱን ከሞት እንዲያድን የኀጢአትንም ብዛት እንዲሸፍን ይወቅ" በማለት ኃጢአት የነፍስ ሞት ንስሐ ደግሞ ሕይወት መሆኑን አስተምሯል (ያዕ5:20)

➝ #ይቀጥላል

https://telegram.me/tewahido_ortho
2.6K views19:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-23 23:42:04 ትንሣኤከ ለእለ አሜነ
ብርሃነ ከፈኖ ድበነ


ዘማር በሱ ፍቃድ አድስ መዝሙር


@Enem_tiwulidnegn
@Enem_tiwulidnegn
@Enem_tiwulidnegn

የእኔምትውልድነኝ ወዳጅች እንኳን ለትንሣኤ ብርሃኑ በረላም አደረሳችሁ
2.6K views20:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-23 11:59:17 በዕፀ መስቀሉ

በዕፀ መስቀሉ የተከፈለልኝ
የኢየሱስ ፍቅር ምንኛ ማረከኝ
ከፍቅርም በላይ ሆነና መሠጠኝ
ከመስቀል ሥር ሁኜ ፊቱን እያየሁኝ

ዓለምን በፍቅሩ ያሸነፈ ጌታ
የጸብን ማዕበል በፍቅሩ የገታ
ሕይወቴን ጸጥ አድርጎ ይምራት በምልሐቱ
እኔ ምን አለፍኝ አልደክምም በከንቱ
#አዝ
ደሙ ከወዙ ጋር ተዋሕዶ ሲወርድ
በእኔ በደል ጌታዬ ቀረብልኝ ለፍርድ
ሀጥያቴን በጫንቃዉ ተሸክሞልኛል
በደሌን ደምሥሶ ንፁሕ አድርጎኛል
#አዝ
የቀራንዮ ግፍ በአንተ ላይ የሆነዉ
ሰይጣንን ጠርቆ ከመንገድ አወጣዉ
እሾሕ አሜኬላዉ ተደምስሶልናል
የንጹሕ በግ ደም አዳምን ታድጓል
#አዝ
ይኽንን ሥጋዬን ብሉ ይላችሁዋል
ይኽንን ደሜንም ጠጡ ይላችሁዋል
ከመስቀል ሥር ሆነን ደሙን እንቀበል
ሥጋዉን እንብላ ሠዉ ሆይ ችላ አንበል

ሊቀ-መዘምራን ይልማ ሀይሉ


ለወዳጅ ያጋሩ

መምህር ምህረተአብ በጅ
ይቀላቀሉ

@tewahido_ortho
2.4K views08:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ