2022-09-01 13:52:55
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በዐሥራ አንደኛው የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ምክር ቤት ጠቅላላ ጉባኤ እየተሳተፈች ትገኛለች።
ነሐሴ 26 ቀን 2014 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ)
++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++
ዐሥራ አንደኛው የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ምክር ቤት ጠቅላላ ጉባኤ በጀመርን ሀገር ካርልስሩሄ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል፡፡ ስብሰባውያን ያዘጋጁት እና ጥሪውን ያስተላለፉት በአውሮፓ የሚገኙ የጀርመን ቤተ ክርስቲያን፣ ቢደን የፕሮቲስታንት ቤተ ክርስቲያን፣ የጀርመን አብያተ ክርስቲያናት ብሔራዊ ጉባኤ፣ የፕሮቴስታንት አብያተ ክርስቲያናት ሕብረት እና የስዊዘርላንድ ቤተ ክርስቲያን በጋር በመሆን ነው፡፡
የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ምክር ቤት ጠቅላላ ጉባኤ የምክር ቤቱ ከፍተኛው የውሳኔ አካል ሲሆን በየስምንት ዓመቱ ይካሄዳል፡፡ በዚህ ስብሰባ የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ምክር ቤት አባል ከሆኑ ከ352 (ሦስት መቶ ሃምሳ ሁለት) አባል አብያተ ክርስቲያናት ውስጥ ሁለት መቶ ዘጠና አምስት አባል አብያተ ክርስቲያናት በተዋካዮቻቸው የተገኙ ሲሆን፣ 800 የሚሆኑ የምክር ቤቱ የባለፈው ማእከላዊና ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴውች አባላት፣ ከ1484 በላይ የምክር ቤቱ ድጋፍ ሰጭና አጋር ተቋማት ተወካዮች፣ 974 የሚሆኑ የምክር ቤቱ ቢሮ ሠራተኞች፣ የአዘጋጁ ሀገር የአስተባባሪ ኮሚቴዎች፣ ከ137 በላይ የሚሆኑ ለመጀመሪያ ጊዜ በጠቅላላ ጉባኤ እየተሳተፉ ያሉ ከመላው ዓለም የመጡ የቦሴ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች፣ ጋዜጠኞች፣ ልዩ ልዩ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች፣ ታዛቢዎች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ፡፡
ስብሰባው በዛሬው እለት ጠዋት የዓለም አብያተ ክርስቲያት ምክር ቤት ዋና ሊቀመንበር (ሞረዴተር) ዶክተር አግናስ አቡም እንኳን ደህና መጣቸችሁ በማለት የከፈቱት ሲሆን ከርሳቸው በመቀጠል የዓለም አብያተ ክርስያናት ምክር ቤት ዋና ጸሐፊ ንግግር አደርገዋል፡፡
በዚህ ስብሰባ የኢትዮጵያ ኦርቶዶከስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ለመጀመሪያ ጊዜ በብፁዕ አቡነ አረጋዊ (ዶ/ር) የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽ/ቤት እና የውጭ ጉዳይ መመሪያ የበላይ ኃላፊ የድሬዳዋና የጅቡቲ አህጉረ ሰብከት ሊቀ ጳጳስ አማካኝነት የማእከላዊና የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል ሁናለች፤ በስብሰባው ላይ የተገኝው የኢትዮጵያ ኦርቶዶከስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ልዑክ በብፁዕ አቡነ ዲዮናስዮስ የጀርመንና አካባቢው ሊቀ ጳጳስ እየተመራ ወደ ስብሰባው ያቀና ሲሆን ከኦሬንታል ኦርቶዶክስ፣ ከምሥራቅ ኦርቶዶክስና ከሌሎች ጥንታውያን አብያተ ክርስቲያናት የተወከሉ ልዑካን በጉባኤው እየተሳተፉ ይገኛሉ ሲል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ዘግቧል፡፡
#Ethiopia
#Tewahedo_Media_Center
#TMC_Addia_Ababa
ተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል
እውነተኛ የተዋሕዶ ድምፅ
የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ
https://youtube.com/channel/UCKqL7UekDOyp6q4j7ObVf9Q
የቴሌ ግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ ፤ ፈጣን መረጃዎችን ያግኙ https://t.me/tewahedomediacenter
አጫጭር ትምህርታዊ እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት የቲክ ቶክ አማራጫችንን ይመልከቱ
https://vm.tiktok.com/ZM8WVucY7/
የኢንስታግራም ገጻችንን
www.Instagram.com/tewahedo_media
477 views10:52