2022-07-15 06:15:04
የትልቅነቱን ያህል ቅርብ እንደ እግዚአብሔር ማን አለ?
“እግዚአብሔር ትልቅ ነው”
መዝሙር 48፥1
ከምደነቅባቸው ህያው ቃሉ መካከል አንዱ፤
"ጌታ ቅርብ ነው "ፊል4:6 የሚለው ነው።
ኃያሉ ልዑል፣ሁሉን ቻዩ ኤልሻዳይ፣የሁሉ ፈጣሪና አስገኝ አዶናይ፣የነበረ ያለ የሚኖር አልፋ ዖሜጋ የሆነው ቅርባችን ነው።
አስባችሁታል ?
ትልቆች የሚገኙት በእነርሱ ሁኔታ እንጂ በእኛ ሁኔታ አይደለም።
ትልቁ እግዚአብሔር በምንም ሁኔታ ብንሆን ቅርባችን ነው።
ሌላው የሚያስደንቀው ቅርብነቱ ለፈለጉት ሁሉ ነው።
ወገኖቼ ትልቅ ሰው፣ሀገር አለ ለሁሉ ግን ቅርብ አይሆንም አይደለምም ።
ለዚህ ነው የምንፈልገውና የምንወደውን ሰው፣ለመርገጥ የምንመኘውን ምድር፣በሕይወታችን አንዴ እንኳ ማግኘት የማንችለው ።
አዎ እግዚአብሔር ታላቅ ነው ለልጆቹ ቅርብ ነው።
ቅርባችን ሁሉን ቻይ ነው ።
ከቅርባችን ጋር ውለን እንደር።
በፊቱ ከምስጋና ጋር በፀሎትና በምልጃ አብረነው ወጥተን እንግባ።
የግልና የቤተሰብ፣የሀገርና የቤተክርስትያን ሐሳባችንን ፣ሸክማችንን ፣የሚያስጨንቀንን ሁሉ ለቅርባችን እንተወውና እንረፍ።
እግዚአብሔር ከእኔና ከአንተ ከአንቺ ጋር ነው!!
ሰው ሁሉ ከማያገኘው የሀገር መሪ ጋር ብንውል ዛሬ ከእገሌ ጋር እያልን ስናወራ ነው የምንውለው ነገም ትላንትና የዋልኩት እያልን መገኘት ሰውኛ ነው።
ካገኘናቸውና ከምናገኛቸው ሁሉ ትልቅ ግን አብረነው ውለን በማደራችን ተደንቀን ያላወራነው አለና ዞር እንበል።
በሉ እስኪ እንዲህ በማለት ዛሬ ስናሰላስል እንዋል እናውራ ።
አንተ የእኔ አባት ከምንልህ ይልቅ ታላቅ ነህ።የገባንን ያህል ነው ትልቅ ነህ የምንልህ አንተ ግን ከዚያም በላይ ነህ።ነገር ግን ከእኔ ከልጅህ ጋር ትገባለህ ትወጣለህ ፤ትሰማኛለህ ትመልስልኛለህ፣አብረኸኝ ስለለህ እጅግ ደስ ይለኛል ተመስገን
እግዚአብሔር ይክበር ይመስገን !!! ተረፈ አበራ
https://t.me/terefeaberaview
297 views03:15