Get Mystery Box with random crypto!

🗞 ጣሀ አህመድ – Taha Ahmed 🗞

የቴሌግራም ቻናል አርማ tahaahmed9 — 🗞 ጣሀ አህመድ – Taha Ahmed 🗞 ጣ
የቴሌግራም ቻናል አርማ tahaahmed9 — 🗞 ጣሀ አህመድ – Taha Ahmed 🗞
የሰርጥ አድራሻ: @tahaahmed9
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.53K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ የተለያዩ ኢስላማዊ ትምህርቶች እና መልእክቶች የሚተላለፉበት መድረክ ነው።
(ወደ መልካም አመላካች እንደ ተግባሪው ምንዳ አለው) በሚለው ነብያዊ ፈለግ መሰረት እርሶም ወደ ኸይር በማመላከትና እርሱን ለሌሎች በማስተላለፍ ስራ የበኩሎን አስተዎፅኦ እንዲያበረክቱ ተጋብዘዎል።
(إن أريد إلا الإصلاح ما استطعت وما توفيقي إلا بالله عليه توكلت وإليه أنيب)

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-08-06 23:27:29 ጣሀ አህመድ – Taha Ahmed pinned a photo
20:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-06 23:26:57 ከዓሹራእ ቀን ጋር ተያያዥነት ያላቸው ቁም ነገሮች

(ክፍል ሁለት)

ከአስረኛው ቀን ጋር አስራ አንደኛውን ቀን መጾም ይህ ከአይሁዶች ጋር ላለመመሳሰል ሲባል የተሻለ ነው:: ይህንን ሀሳብ ከዓሹራእ ቀን በፊት ወይም በኋላ መጾምን በተመለከተ የተዘገበውን ደካማ ሀዲስ መሰረት በማድረግ ሳይሆን ከላይ ያሳለፍነው እና መሰል አይሁዶችን መቃረንን የሚያመላክቱ ሀዲሶችን ሀሳብ እንዲሁም በዚህ ወር ጾምን ማብዛት የተወደደ መሆኑን መሰረት በማድረግ ነው::
አስረኛውን ቀን ብቻ መጾምን በተመለከተ ከላይ በመጀመሪያ የጠቅስነውን ሀዲስ መረጃ በማድረግ አብዛኞቹ ዑለማዎች የዓሹራእን ቀን ብቻ መጾም አይጠላም ብለዋል::
የዓሹራን ቀን በተመለከተ ከመጾም ውጪ በዚህ ቀን የተለየ የሚደረግ ማንኛውም አምልኳዊም ሆነ ሌላ የተለየ ተግባር በመልእክተኛው ሱና ውስጥ ምንም አይነት መሰረት የሌለው መሆኑን እና በዚህ ቀን በተለየ መልኩ እንዲህ ማድረግ ይወደዳል እንዲህ ማድረግ ይገባል በሚል የሚወሩ የተለያዩ ነገሮች ትክክለኛ መሰረት ያላቸው ሀዲሶችን የተመረኮዙ አለመሆናቸውን አውቆ ሙስሊሙ ማህበረሰብ በትክክለኛ እና ጠንካራ ሀዲስ ላይ የተመሰረተውን ጾም በመጾም ወደ አላህ እንዲቃረብ ዑለማዎች በአንክሮ ይመክራሉ።

በመጨረሻም ማንኛውም ነገ አላህ ፊት ቀርቤ ስራዬን እመረመራለሁ ስለዚህ መልካም ስራን ሰርቼ ከጌታዬ ጋር መገናኘት እፈልጋለሁ የሚል ሰው የሚሰራውን ስራ ለአላህ ብቻ አጥርቶ በኢኽላስ ሊሰራ እንዲሁም የአላህ እና የመልእክተኛው ትእዛዝ ካለበት ተግባር ውጪ ሌላን ስራ ከመስራት ሊርቅ ይገባል::
ሁላችንም ልብ ብለን የእነዚህን ሁለት ሀዲሶች መልእክት እንድናስተንትን እጋብዛለሁ: –
የአላህ መልእክተኛ ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል:-"በዚህ በዲናችን ላይ ከርሱ ያልሆንን ያመጣ ሰው ስራው ተመላሽ ነው፡፡" (ቡኻሪ እና ሙስሊም ዘግበውታል)
በሌላው ሀዲስ ላይ የአላህ መልእክተኛ ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል:-"ማንኛውም ስራ የሰራ በዚያ ስራ ላይ የእኛ ትእዛዝ ከሌለበት ስራው ተመላሽ ነው፡፡" (ቡኻሪ እና ሙስሊም ዘግበውታል)

አላህ መልካም ሰራን ከሚሰሩት እና ከሚቀበላቸው ያድርገን!

ጣሀ አህመድ (ሙሐረም 1442 የተፃፈ)

https://t.me/tahaahmed9
373 views20:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-06 23:26:57
ከዓሹራእ ቀን ጋር ተያያዥነት ያላቸው ቁም ነገሮች

የአላህ መልእክተኛ ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል:- "የዓሹራእ ቀንን መጾም ያለፈውን አመት ወንጀል ያሳብሳል ብዬ አላህ ላይ ተስፋ አደርጋለሁ::" (ሙስሊም ዘግበውታል)
የዓሹራእ ቀን ከሙሐረም ወር አስረኛው ቀን ነው:: በዚህ እለት ነበር አላህ ነብዩ ሙሳ እና ህዝባቸውን ከፊርዓውን ያዳናቸው::
የዓሹራእን ቀን መጾም የተወደደ ስለመሆኑ ዑለማዎች ስምምነት ኢጅማዕ ያላቸው መሆኑን ነወዊ እና ኢብኑ-ሐጀር እንዲሁም ሌሎችም ዘግበዋል::
የረመዳን ወርን መጾም ግዴታ ከመሆኑ በፊት ይህን ቀን መጾም ግዴታ የነበረ ሲሆን ከዚያ በኋላ ግን ግዴታነቱ ተሽሮ በፍላጎት የሚጾም የሱና ጾም ሆኗል::
በአራቱም መዝሀብ ዑለማዎች አቋም መሰረት ከዓሹራእ ቀን በተጨማሪ ዘጠነኛውንም ቀን መጾምም ይወደዳል:: ይህም መልእክተኛው ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም አይሁዶች እና ክርስቲያኖች ይህንን ቀን እንደሚያክብሩት በሰሙ ግዜ እንዲህ በማለታቸው ነው:- "በአላህ ፍቃድ እስከ ሚቀጥለው አመት ከቆየሁ ዘጠነኛውንም ቀን አብረን እንጾማለን::" (ሙስሊም ዘግበውታል)
ከዓሹራእ ቀን ጾም ጋር በተያያዘ ዑለማዎች የተለያዩ መረጃዎችን በመመርኮዝ በዚህ መልኩ ቢሆን የተሻለ ነው ሲሉ የሚሰነዝሮቸው ሀሳቦች አሏቸው ከነዛም መካከል የተወሰኑትን ለመጠቆም ያህል:-
ዘጠነኛውን ቀን ከአስረኛው ቀን ጋር መጾም አስረኛውን ቀን ብቻ ከመጾም የተሻለ ነው:: ከላይ ያሳለፍነው "በአላህ ፍቃድ እስከ ሚቀጥለው አመት ከቆየሁ ዘጠነኛውንም ቀን አብረን እንጾማለን::" የሚለው ሀዲስ ይህንን ሀሳብ ያጠናክራል::

ይቀጥላል…

https://t.me/tahaahmed9
330 views20:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-11 06:47:02 በሚዳሰሱ ሞዴሎች ሐጅና ኡምራን ማስተማር እንዴት ይታያል?

ከቅርብ አመታት ወዲህ የሐጅ አፈፃፀም ስርአትን ለህፃናት በማስተማር አላማ የሚዘጋጁ ፕሮግራሞች ተበራክተዋል። የአዘጋጆቹ ሀሳብ መልካም ቢሆንም በሸሪዓ እንዴት ይታያል የሚለውን ማጥናት ተገቢ ይሆናል። ከዚህ አንፃር የፕሮግራሞቹ አዘጋጆች ጉዳዩን ትኩረት ሰጥተው እንዲያጤኑት ጥሪዬን አቀርባለው።

ይህ የማስተማሪያ ዘዴ በተለያዩ ሀገራት የተተገበረ በመሆኑ ብይኑን በተመለከተ ኡለማዎች ትኩረት ሰጥተው ውይይትና ምክክር አድርገውበታል። ምንም እንኳ አላማውን በመመልከት ይቻላል ያሉ አንዳንድ ኡለማዎች ቢኖሩም አብዛኞቹ ኡለማዎች እና የፈትዋና የምርምር ተቋማት ግን እንደማይፈቀድና ተገቢም እንዳልሆነ ገልፀዋል።

የዓለም የፊቅህ ሊቃውንት ምክር ቤት (መጅመዕ አልፊቅህ አልኢስላሚ) በሒጅራ አቆጣጠር ከሻዕባን 5/1412 እ.ኤ.አ በ 8/2/1992 ጀምሮ ባደረገው አስራ ሶስተኛ መደበኛ ጉባኤው የካዕባ ሞዴል በመስራት ልጆችን ማስተማርን በተመለከተ ተወያይቶ ባሳለፈው ውሳኔ (ይህ ተግባር ክልክል ወደሆኑ ክፉ ነገሮች ሊያዳርስ ስለሚችል መከልከልና በር መዝጋት ዋጂብ መሆኑን) አፅንቷል።
[ቀራራት አልመጅመዕ ገፅ 285]

እንደዚሁ የሳውዲ ቋሚ የፈትዋ ኮሚቴም (ካዕባ፣ መቃሙ ኢብራሂም፣ ጀመራት እና መሰል ቦታዎችን በሚዳሰስ ሞዴል በመስራት የሐጅና ዑምራ ክንዋኔዎችን ማስተማር አየፈቀድም) ካሉ በኋላ ምክንያቶችን ሲጠቅሱ፤ ሞዴሎቹን ማላቅ ወይም ማዋረድን የመሳሰሉ መጥፎ ውጤቶችን ሊያስከትል ይችላል ብለዋል። ገላጭ የሆኑ ፅሁፎችን በማብራራት ለሰፊው ህዝብ በቂ በሆነ መልኩ ማስተማር ስለሚቻል ሞዴል መስራት አስፈላጊ እንዳልሆነ ተናግረዋል።
[ፈታዋለጅናህ 14/11]

ታላቁ አሊም ሸይኽ ኢብኑ ኡሰይሚንም በዚህ መልኩ ማስተማር የማይገባና የማይፈቀድ እንደሆነ በመግለፅ በምትኩ ቦርድ ላይ የካዕባን ስእል በመሳል ጠዋፍ እንደሚደረግ ማስተማር እንደሚቻል ተናግረዋል። በሞዴል ማሳየት በቀልብ ውስጥ ለኢባዳው ያለንን ቦታ በማሳጣት እንቅስቃሴ ብቻ ያደርገዋል ብለዋል።
[መጅሙዕ ፈታዋ ቅፅ 24 ገፅ 91]

በሞዴል ማስተማር ይቻላል ያሉ አንዳንድ ኡለማዎችም ቢሆን የዚህ አይነቱ ትምህርት በኢስላማዊ ጉዳዮች ሚኒስቴር (ዊዛራ) ክትትል ሊፈፀም እንደሚገባ ከመጠቆማቸው ጋር ሞዴሎቹ እውነተኛውን የካዕባና የሐጅ ክንውን ቦታዎችን በጣም የማስመሰል ስራ እንዳይሰራ ከልክለዋል። እንደውም ሞዴሎቹ ትንንሽ ሆነው በአካባቢውና በያንዳንዱ ሞዴል ላይ መማሪያ መሆኑ እንዲገለፅበት፣ እንደ ኢባዳ ሳይሆን እንደ ትምህርት መማሪያ ብቻ መሆኑ ተደጋግሞ እንዲነገርና የሞዴሎቹን ክብር ከመንካት መጠንቀቅና ሌሎች መስፈርቶችን አስቀምጠዋል።

የእነዚህ ፕሮግራሞች አላማ የኢባዳው ፍቅር በልጆች ልቦና እንዲያድር ማድረግ እንጂ በዚህ እድሜ የሐጅ አፈፃፀም ህግጋትን የማወቃቸው አስፈላጊነት ጎልቶ አይመስለኝም። የሚዳሰሱ ሞዴሎችን በመገንባት ማስተማር የኡለማዎችን ትችት ያስተናገደና ቢያንስ በሸሪዓ ስለመፈቀዱ አጠራጣሪ የሆነ የማስተማሪያ መንገድ ነው። የሚያጠራጥርን ነገር በመተው ታዘናልና አዘጋጆች ሌሎች የማስተማሪያ መንገዶችን ቢጠቀሙ የተሻለ ይሆናል። ለምሳሌ ዘመናዊው ቴክኖሎጂ ባመጣቸው እንደ 3D፣ ፓወር ፖይንትና እና ሞሽን ግራፊክስ በመጠቀም ማስተማር ይቻላል። ከዚህም በተሻለ በተቀረፀ እውነተኛ የሐጅ አፈፃፀም ቪድዮ ማስተማር ቀላል ነው። ወላሁ አዕለም

{إِنۡ أُرِیدُ إِلَّا ٱلۡإِصۡلَـٰحَ مَا ٱسۡتَطَعۡتُۚ وَمَا تَوۡفِیقِیۤ إِلَّا بِٱللَّهِۚ عَلَیۡهِ تَوَكَّلۡتُ وَإِلَیۡهِ أُنِیب}
በተቻለኝ ያክል ማበጀትን እንጂ አልሻም። (ለደግ ሥራ) መገጠሜም በአላህ እንጂ በሌላ አይደለም፡፡ በእርሱ ላይ ተመካሁ፡፡ ወደ እርሱም እመለሳለሁ» አላቸው፡፡
[Surah HĂťd: 88]

ሐምሌ 3/2014

አቡጁነይድ ሳላህ አህመድ


http://T.me/abujunaidposts
719 views03:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-10 17:10:18
አላህን ማመስገን!

የአላህ መልእክተኛ ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል:– "አላህ ባሪያው ጥቂት ምግብን በልቶ እንዲያመሰግነው እንዲሁም ጥቂትን ጠጥቶም እንዲያመሰግነው ይወዳል።" (ሙስሊም ዘግበውታል)

ኢማሙ አንነወዊ አላህ ይዘንላቸው ይህን ሐዲስ ሲያብራሩ "ጥቂት ምግብ" በሚለው ቃል ለማለት የተፈለገው እንደ ቁርስ ወይም እራት ያለውን አንድ የምግብ ወቅት መብል እንደሆነ ገልፀው፤ ሀዲሱ ከመብላት እና መጠጣት በኃላ አላህን ማመስገን እንደሚወደድ ያስረዳል ብለዋል።

የምስጋናው አባባልም በቡኻሪ እንደተዘገበው
 «الحمدُ للهِ حمْدًا كثيرًا طيِّبًا مُباركًا فيه، غيرَ مَكفِيٍّ ولا مُودَّعٍ ولا مُستَغنًى عنه ربَّنا»
"አልሀምዱ ሊላህ ከሲረን ጠይበን ሙባረከን ፊሂ ገይረ መክፊዬ ወላ ሙወዲዒ ወላ ሙስተግኒ ዓንሁ ረበና" ቢሆን የተሻለ እንደሆነ ገልፀዋል። ነገር ግን

 «الحمدُ للهِ»
"አልሀምዱ ሊላህ" ካለም በቂ እንደሚሆን አብራርተዋል።

ጣሀ አህመድ

https://t.me/tahaahmed9
541 views14:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-10 15:02:21
ከዙል–ሒጃ ወር 11ኛው፣ 12ኛው እና 13ኛው ቀናት

የአላህ መልእክተኛ ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል:– "አያሙ አት‐ተሽሪቅ (ከዙል‐ሒጃ ወር 11ኛው፣ 12ኛው እና 13ኛው ቀናት) የመብላት፣ የመጠጣት እና አላህን የማውሳት ቀናት ናቸው።" (ሙስሊም ዘግበውታል)

መልእክተኛው ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም በዚህ ሐዲስ በነዚህ ቀናት የምንፈፅማቸውን ዋነኛ ነገሮች ጠቁመውናል። ትኩረት ልናድረግበት እና ልንተዋወስበት የሚገባው ትልቁ ነገር አላህን ማውሳት (ዚክር ማድረግ) እንዲሁም እርሱ በእኛ ላይ የዋለውን ውለታ በማስታወስ ማመስገን ነው። ይህን የሚታደሉ ጥቂቶች ናቸው።

አላህ እርሱን ለማስታውስ፣ ለማመስገን እና አሳምሮ ለማመለክ ይርዳን!

ጣሀ አህመድ

https://t.me/tahaahmed9
456 views12:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-09 09:59:57
መብላት፣ መጠጣት እና መልበስ እሰከ የት ድረስ ሊሆን ይገባል?

የአላህ መልእክተኛ ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል:– " ብሉ፣ ጠጡ፣ ምፅዋትን ስጡ እንዲሁም ልበሱ ይህን ድርጊታችሁን ድንበር ማለፍ ወይም ኩራት እሰካልተቀላቀለው ድረስ።" (ሀዲሱን ነሳኢ ዘግበውታል አልባኒም ሀሰን ብለውታል)

ኩራት (መኺላ):– የሚለው ቃል ትርጉም በዚህ አገባቡ ልታይ ማለትን እና በራስ ድርጊትም ይሁን ማንነት መገረምን ያካትታል።

ጣሀ አህመድ

https://t.me/tahaahmed9
512 views06:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-08 19:43:15 የዒድ አከባበር ደንቦች

ክፍል 3

ከዒድ ጋር በተያያዘ የሚፈፀሙ ስህተቶችን በተመለከተ ከክፍል ሁለት የቀጠለ።

ኛ. ባዕድ በሆኑ ወንዶችና ሴቶች መካከል መቀላቀል፤ አልፎም መጨባበጥና መሳሳም፡፡ ይህ ሸሪዓው ክፉኛ የኮነነው ተግባር ነው፤ የአላህ መልእክተኛ (ሰላትና ሰላም በርሳቸው ላይ ይሁን) ከእለታት አንድ ቀን ከመስጂድ በመውጣት ላይ ሳሉ ወንዶች ከሴቶች ጋር በመንገድ ላይ ተቀላቅለው ተመለከቱ ይህንን ክስተት በማስመልከትም "ከወንዶች ወደ ኋላ ሁኑ፤ የመንገዱንም መሀከል ይዛችሁ ልትጓዙ አይገባም" አሉ፡፡ ይህንን ሀዲስ የዘገበው ሰሃቢይ "ከዚህ በኋላ ሴቶች በጣም ወደ ዳር ከመውጣታቸው ልብሳቸው በአጥር ይያዝ ነበር፡፡" በማለት ይናገራል፡፡(አቡዳውድ ሱነናቸው ላይ ሲዘግቡት አልባኒ ሀሰን የሚል ደረጃ ሰጥተውታል) ይህ ሀዲስ ሸሪዓ በጥቅሉ ወደ ሀራም የሚያደርሱ ነገሮችን የከለከለ መሆኑን ከሚያሳዩ መረጃዎች አንዱ ነው፡፡
በሌላ ሀዲስ የአላህ መልእክተኛ (ሰላትና ሰለም በርሳቸው ላይ ይሁን) "እኔ ሴቶችን አልጨብጥም" ማለታቸው ሰፍሯል፡፡ ሀዲሱ አንድ ሰው ምንም እንኳ የተቀደሰ አላማና ንፁህ ልቦና ነው የያዝኩት ቢልም ባዕድ ሴቶችን ከመጨበጥ ሊቆጠብ እንደሚገባ የሚያመለክት ነው፡፡
ኛ. እንደ ሙዚቃ እና መሰል የተከለከሉ ነገሮችን ከማድመጥ፣ ፊልሞችን በመመልከት ጊዜን ከማጥፋት መቆጠብ ያስፈልጋል:: እንዲሁም ሌሎችንም ሀራም የሆኑ ተግባራትን በሙሉ መጠንቀቅ ይገባል::
ኛ. በዒድም ይሁን በሌላ ጊዜ በኢስላም ማባከን እጅጉን የተኮነነ ተግባር ቢሆንም በዒድ እለት በአንዳንዶች ዘንድ ከሚታዩት ስህተቶች መካከል ምግብና መጠጥን ማባከን ነውና ልንርቀው ይገባል::
ኢስላም በራሱ የተሟላ ነው!
እንደሚታወቀው ሀይማኖታችን ኢስላም ምሉዕ ነው፡፡ ስለሆነም ለሁሉም የአምልኮ ዘርፎች እንዲሁም የህይወት መስኮች ደንቦችን ደንግጓል ስርዐቶችንም አስቀምጧል፡፡ ሕግጋቶቹ ፍትሀዊ እና ሚዛናዊ ስርዐቶቹም ለሁሉም ቦታ እና ዘመን የሚበጁ ናቸው፡፡ አላህ (ሱብሀነሁ ወተአላ) እንዲህ ይላል:-
{الْيَوْمَ أَكْمَلْتُ لَكُمْ دِينَكُمْ وَأَتْمَمْتُ عَلَيْكُمْ نِعْمَتِي وَرَضِيتُ لَكُمُ الْإِسْلَامَ دِينًا} المائدة 3

‹‹ዛሬ ሐይማኖታችሁን ሞላሁላችሁ፤ ፀጋዬንም በእናንተ ላይ ፈፀምኩ፤ ከሀይማኖት በኩልም ለእናንተም ኢስላምን ወደደኩ...›› (አልማኢዳ፡ 3)
ከዚህም በመነሳት መጨመርንም ይሁን መቀነስን አይቀበልም እንዲሁም ከሌሎች መኮረጅንም ሆነ መመሳሰልን ይከለክላል፡፡
ይህንን እዉነታ የአላህ መልእክተኛ (የአላህ ሰላምና ሰላት በርሳቸው ላይ ይሁን) በነዚህ ሁለት ነብያዊ አስተምህሮቶች ይገልፁታል፡፡

قال رسول الله صلى الله عليه وسلم : ( من أحدث في أمرنا هذا ما ليس منه فهو رد ) رواه البخاري (2697) ومسلم (1718)

"በዚህ በዲናችን ላይ ከርሱ ያልሆንን ያመጣ (ሰው) ስራው ተመላሽ ነው፡፡ (ተቀባይነት አይኖረውም)" (ቡኻሪ እና ሙስሊም ዘግበውታል)

قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ : ( مَنْ تَشَبَّهَ بِقَوْمٍ فَهُوَ مِنْهُمْ ) رواه أبو داود (4031)

"ከህዝቦች የተመሳሰለ እረሱ ከነርሱ ነው፡፡" (አቡ ዳውድ ዘግበውታል)
ስለሆነም ዒዳችንን ስናከብርም ይሁን ማንኛውንም አይነት ዒባዳ ስንፈጽም ከጭማሪ (ቢደዓ) እራሳችንን ልናርቅ እንዲሁም በማነኛውም የህይወታችን ክፍሎች ከሌሎች ጋር መመሳሰልን ትተን ሙሉ የሆነውን ሸሪዓን በማወቅ ወደ ተግባር ልንለውጥ ይገባል::

تقبل الله منا ومنكم صالح الأعمال.

አላህ መልካም ስራችንን ይቀበለን!!

*ጣሀ አህመድ (1431ሂ) የተፃፈ*


https://t.me/tahaahmed9
410 views16:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-08 19:42:49 የዒድ አከባበር ደንቦች

ክፍል 2

የተክቢራ አፈፃፀም

ከመልክተኛው ትክክለኛ ሰነድን መሰረት ያደረገ እና የተክቢራን አባባል ዝርዝር ሁኔታ የሚገልፅ መረጃ ባይገኝም ከሰሀቦቻቸው ግን "አላሁ አክበር አላሁ አክበር ወሊላሂልሀምድ" እና የመሳሰሉት አባባሎች በትክክለኛ ሰነድ ተዘግበዋል፡፡ ስለሆነም ሙስሊሞች እነዚህን አባባሎች የትኞቹ እንደሆኑ ማጥናትና እነርሱን ማዘውተር ይጠበቅባቸዋል፡፡ ኢብኑ ሀጀር አል-ዓስቀላኒ ፈትሁል-ባሪ በተሰኘው ኪታባቸው እንዲህ ይላሉ "በዚህ ዘመን (ተክቢራን በተመለከተ) ብዙ መሰረት የሌላቸው ጭማሪዋች ተከስተዋል፡፡" ይህ በሂጅራ አቆጣጠር (ከ773-852) የኖሩት የኢስላም ሊቅ ንግግር ነው። ታዲያ ባለንበት ዘመን ምን ያህል ጭማሪ ተከስቶ ሊሆን እንሚችል ስናስተውል በጉዳዩ ላይ ከባድ ጥንቃቄ ልናደርግ እንደሚገባ ያመላክተናል፡፡
በአንድ ድምፅ ወይም አንድን ሰው አዝማች (አውጪ) ሌላው ተቀባይ ሆኖ የሚደረግ ተክቢራም ሱናን የሚቃረን ተግባር ነው። በዚህ ዙሪያ ተምሳሳይ ድርጊት ከሚፈጽሙት ወገኖች እንደ መረጃ የሚጠቀሰው የዑመር ተግባር (ሚና ላይ በድንኳን ውስጥ ሆኖ ድምፁን ከፍ አድርጎ ተክቢራ ሲያደርግ ሰዎችም ተክቢራውን ሰምተው ተክቢራን ማድረጋቸው) የሚያመለክተው የእሱን ድምፅ ሲሰሙ ተክቢራን ማድረግ እንዳለባቸው በማስታወስ እነርሱም ተክቢራ ያደርጉ እንደነበረ እንጂ ሌላን አይደለም። ስለሆነም ይህ ክስተት፤ በጋራ ድምፅ እርሱን እንደ አዝማች እነርሱ እንደ ተቀባይ ሆነው ይቀጥሉ ነበር የሚለውን እንድምታ አያስጨብጥም ሲሉ ዑለማዎች ይናገራሉ፡፡

ጥቂት ከዒድ ጋር በተያያዘ የሚፈፀሙ ስህተቶች

ኛ. ዒድ መሆኑ ከታወቀበት ሰአት ጀምሮ ወንዶች ከሰላተል ጀመዓ መቅረት ብሎም በረመዳን ሲሰግዱት የነበረውን ዊትር ሰላት ማቋረጥ፤ አንዳንዴም አምልኮዎች በዚህ ያበቃሉ የተባለ ይመስል እርግፍ አድርጎ መተው ይስተዋላል፡፡
ኛ. የዒዱን ዋዜማ ለሊት በተለያዩ ዒባዳዎች ህያው ማድረግን በተመለከተ የመጡት ሀዲሶች ከሰነድ አንፃር ደካማዎች ናቸው፡፡ በሌላ በኩል ለሊቱን በተለያዩ የሚጠቅሙም ይሁን ያማይጠቅሙ ነገሮች ላይ ማሳለፍ፤ በዚህም የተነሳ የፈጅር ሰላትን አለመስገድ እና ሰላተል-ዒድን እንደ ቀላል በመመልከት ችላ ብሎ መተው::
የዒድ ሰላትን በተመለከተ "ሰላተል-ዒድ በእያንዳንዱ ግለሰብ ላይ በነፍስ ወከፍ ግዴታ ነው" የሚለው የአቡ ሀኒፋ አቋም ሲሆን ከኢማሙ አሻፊዒይ እና አህመድም ከተዘገቡት ሁለት የተለያዩ አቋሞች አንዱ የሚጠቁመውም ይህንኑ ነው። ሸይኹል-ኢስላም ኢብኑ-ተይሚያህ እና ሌሎች ብዙ ዑለማዎችም ይህን አቋም የሚደግፉ መሆኑን መረዳት ያስፈልጋል፡፡
ኛ.በአለባበስና መቆነጃጀት ዙሪያ ከሚከሰቱ ስህተቶች መካከል ብዙ ወንዶች ፂማቸውን መላጨትና ማሳጠር እንዲሁም ልብሳቸውን ከቁርጭምጭሚታቸው በታች እነዲወርድ በማድረግ የሚፈፅሙት ስህተት ይገኝበታ። ሴቶች ደግሞ ሽቶን በመቀባት በመገላለጥ የሚፈፅሙት ስህተት እጅግ አደገኛ ነው፡፡ እነዚህን ጉዳዮች በተመለከተ የመጡት ነብያዊ አስተምህሮቶች በጣም አስፈሪና አስደንጋጭ ናቸው፡፡

عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ رَضِيَ اللَّهُ عَنْهُ عَنْ النَّبِيِّ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ قَالَ : ( مَا أَسْفَلَ مِنْ الْكَعْبَيْنِ مِنْ
الْإِزَارِ فَفِي النَّارِ) رواه البخاري (5787)

ከአቡሁረይራ በተላለፈ ሀዲስ የአላህ መልዕክተኛ እንዲህ ብለዋል:- "ከሽርጥ ከቁርጭምጭሚት የወረደዉ የእሳት ነው" (ቡኻሪና በቁጥር (5787) ዘግበዉታል)
ይህ ሁሉንም የልብስ አይነት እንደሚያካትት ለመግለፅ አል-ኢማም አል-ቡኻሪይ ለሀዲሱ "ከቁርጭምጭሚት የወረደው እሱ የእሳት ነው" የሚል ርዕስ ሰጥተውታል።
በሌላ ሴቶች ከቤት ሲወጡ ምን አይነት ስነ-ስርአት መከተል እንደሚገባቸው በሚጠቁም ሀዲስ ላይ የአላህ መልዕክተኛ እንዲህ ብለዋል:-"ማንኛዋም ሴት ሽቶን ተቀብታ ወደ መስጂድ የወጣች እንደሆነ እስክትታጠብ ድረስ ሰላቷ ተቀባይነት የለውም፡፡"(ኢብኑ ማጃህ እና አህመድ ዘግበውታል አልባኒም ሰሂህ መሆኑን ገልፀዋል፡፡)

عن أبي هريرة قال: قال صلى الله عليه وسلم : "صِنفانِ مِن أهلِ النارِ لم أرَهما..... ونِساءٌ كاسياتٌ عارياتٌ مميلاتٌ مائلاتٌ، رؤوسُهُنَّ كأسنِمَةِ البُخْتِ المائلةِ لا يَدْخُلْنَ الجنةَ ولا يَجِدْنَ رِيحَهَا، وإن رِيحَهَا لَيوجَدُ مِن مَسيرةِ كذا وكذا". رواه مسلم(2128)

ሙስሊም አቡ ሁረይራን ዋቢ አድርገው ባስተላለፉት ሀዲስ ላይ የአላህ መልዕክተኛ እንዲህ ብለዋል:- "ከእሳት ሰዎች መካከል ሁለት አይነት ሰዎች በእኔ (ዘመን) አላየኋቸውም (ወደፊት ይመጣሉ)" አሉና፤ የመጀመሪያዎቹ ምን አይነት ባህሪ እንዳላቸው ካብራሩ በኋላ "ሌለኞቹ ሴቶች ናቸው፤ ለብሰው ያልለበሱ አካሄዳቸው እና እንቅስቃሴያቸው ወደርካሽ አላማ ያዘነበለ፤ ሌሎችንም የሚያሳስቱ ፀጉራቸው ልክ እንደ ግመል ሻኛ የተከመረ ናቸው:: እንደነዚህ አይነቶቹ ጀነትን አይገቡም ሽታዋንም አያገኙትም" አሉ::

ክፍል 3 ይቀጥላል.…

*ጣሀ አህመድ (1431ሂ) የተፃፈ*

https://t.me/tahaahmed9
307 views16:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-08 19:36:03 * የዒድ አከባበር ደንቦች *

ክፍል 1

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩህሩህ በጣም አዛኝ በሆነው::
ምስጋና ለአለማት ጌታ ለአላህ የተገባ ነው፡፡ የአላህ ሰላትና ሰላም በመልእክተኛው ሙሀመድ፤ በቤተሰቦቻቸው እና በባልደረቦቻቸው ላይ ይሁን፡፡

* ዒድ ማለት ምን ማለት ነው? *

ኢብኑል-ዓረቢይ ዒድ "ዒድ" ተብሎ ስለመሰየሙ ሲናገሩ በየአመቱ አዲስ ደስታን ይዞ የሚመለስ ከመሆኑ አንፃር መሆኑን እና "ዓደ" (ተመለሰ) ከሚለው ቃል የተወሰደ መሆኑን ይገልፃሉ፡፡ እዚህ ላይ ልብ ልንልን የሚገባው ዒድ ቂያማ እስኪቆም ተመላልሶ የሚመጣ ቢሆንም እኛ ግን የሚቀጥለውን ለመድረስ ምንም ዋስትና እንደሌለን ነው፡፡ ስለሆነም ከአላህ ህግ ፈፅሞ ልንወጣ አይገባም፡፡

አነስ ኢብኑ ማሊክ እንዲህ ይላሉ:- ‹‹የአላህ መልእክተኛ (ሰላትና ሰላም በርሳቸው ላይ ይሁን) መዲና ከተማ ሲመጡ የመዲና ሰዎች በመሀይምነት ዘመን (ደስታቸውን የሚገልፁባቸው) የሚጫወቱባቸው ሁለት ክብረ-በዓላት ነበሮቸው። ይህንን ባዩ ጊዜ የአላህ መልእክተኛ እንዲህ አሉ፡፡ "አላህ በእነዚህ በሁለቱ ምትክ ከእነርሱ የተሻሉ ሁለት ክብረ-በዓላትን ቀየረላችሁ፤ እነሱም "የፊጥር" እና "የአድሀ" በዓላት ናቸው፡፡" (አቡዳውድ እና አህመድ ዘግበውታል)
ከዚህ ሀዲስ ዑለማዎች የተረዷቸዉን ሁለት ቁም ነገሮች ልናስተውል ይገባል።
አንደኛ፡- ከእስልምና ውጭ ካሉ ማህበረሰቦች ጋር መመሳሰል የተከለከለ መሆኑ::
ሁለተኛ ፡- በኢስላም የተደነገጉ ክብረ-በዓላት ሁለት ብቻ መሆናቸውን ነው::

* ከዒድ ዋዜማ ጀምሮ ልንፈፅማቸው የሚገቡ ነገሮች *

ከዚህ በላይ በአጭሩ ዒድ ማለት ምን ማለት እንደሆነና በኢስላም የተደነገጉ ክብረ-በዓላት ዒድ-አልፈጥር እና ዒድ-አልአድሀ ብቻ መሆናቸውን ከተረዳን፤ በእነዚህ ሁለት ዒዶች ዋዜማ እና በእለቱ ምን ማድረግ ይወደዳል? ምንስ ይፈቀዳል? ምን ከማድረግ ልንከለከል ይገባል? ወደ ሚሉት ነጥቦች እንሂድ፡፡

በመጀመሪያ ከዒድ ዋዜማ ጀምሮ ልንፈፅማቸው ከሚያስፈልጉ ነገሮች:-
በዒደል-ፊጥር ዒድ መሆኑ ከተረጋገጠበት ሰአት አንስቶ ሰላቱ እስኪጀመር በዒደል-አድሀ ደግሞ ከዙል-ሂጃ የዘጠነኛው እለት ፈጅር ሰላት አንስቶ የአስራ ሶስተኛው እለት ፀሀይ እስከትጠልቅ ድረስ ተክቢራን ማድረግ ይገባል፡፡
መታጠብ እራስን ማሰማመር እና ከልብሶች መካከል የተሻለውን እና ቆንጆውን መልበስ ከሰለፎች የተዘገበ ተግባር ነው፡፡
ሴቶችን በተመለከተ በዚህ እለትም ይሁን በሌላ ጊዜ ከቤታቸው እንዴት መውጣት እንዳባቸው በሸሪዓ የታወቀ ነው፡፡ እናም ከመገላለጥ እና ሽታ ያላቸውን ነገሮች ተጠቅመው ከመውጣት ተቆጥበዉ ከቤታቸው ወደ መስጊድ ወይም ወደ ዒድ መስገጃ ስፍራ ሊሄዱ ይገባል፡፡
የአላህ መልእክተኛ (የአላህ ሰላትና ሰላም በርሳቸው ላይ ይሁን) ለጋብቻ የቀረቡና የደረሱ እንዲሁም በወር አበባ ላይ ያሉ ሴቶችን ጨምሮ ወደ ዒድ ሰላት መስገጃ ቦታ ስፍራ እንዲወጡ ትዕዛዝ ማስተላለፋቸውን ተከትሎ እንዲህ የሚል ጥያቄ ተጠይቀው ነበር ‹‹አንዳችን ጅልባብ ባይኖራት ምን ታድርግ?›› እሳቸውም እንዲህ አሉ ‹‹እህቷ (ጓደኛዋ) ታውሳት(ታልብሳት)››(ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል)
በሌላውም ሀዲስ እንዲህ ብለዋል ‹‹ሴቶችን መስጊድ ከመሄድ አትከልክሏቸው ነገር ግን ከቤታቸው ሽታ ያለው ነገርን ተጠቅመው እንዳይወጡ፡፡››(አል-ኢማም አህመድና አቡዳውድ ሲዘግቡት አልባኒ ሰሂህ ብለውታል)
በዒደል-ፊጥር ሰጋጁ ወደ መስገጃው ከመውጣቱ በፊት ዊትር (አንድ፤ ሶስት፤ አምስት …..) ቁጥር ያላቸውን ተምሮች በልቶ ወደ ዒድ መስገጃው መሄድ።
ለዒድ ሰላት ከመሄድ በፊት ዘካተል-ፊጥርን ለተገቢው ወገን መስጠት።
የዒድ ሰላትን ለመስገድ ከፍተኛ ፍላጎትና ጉጉት ሊኖር ይገባል። ምክንያቱም ይህ ተግባር ከታላላቅ የኢስላም መገለጫዎች አንዱ ከመሆኑም ባሻገር የአላህ መልእክተኛ (ሰላትና ሰላም በእሳቸው ላይ ይሁንና) የዒድ ሰላትን ከተደነገገበት ጊዜ አንስቶ እስከ ሕልፈታቸው ትተውት አያውቁም ነበር። ከዚህ በተጨማሪም በመሰረቱ ሰላትን መስገድ የተከለከሉትን የወር አበባ ላይ ያሉ ሴቶች ሳይቀር በቦታው ላይ እንዲገኙ አዘዋል፡፡
ሰላቱ ከተጠናቀቀ በኋላ በተቻለ አቅም ኹጥባን ማዳመጥ።
ወደ ዒድ ሰላት ከሄዱበት መንገድ በሌላ መንገድ መመለስ።
የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት መለዋወጥ፡፡ ይህም ”ተቀበለላሁ ሚና ወሚንኩም" የሚል ሲሆን የተለያዩ የኢስላም ሊቃውንት ከሰሃቦች መገኘቱን አረጋግጠዋል።
ከዒደል-ፊጥር ጋር በተያያዘ ዘካተል-ፊጥርን መስጠት መታዘዙ የተለያዩ ችግረኞችን ማስታወስ እና አቅም በፈቀደ መጠን ችግራቸውን ለመቅረፍ ጥረት ማድረግ የሚደገፍ ተግባር መሆኑን የሚያመለክት ነው።
በአጠቃላይ ሸሪዓው ያዘዘባቸውን እና የፈቀዳቸውን ተግባራት መፈፀም የሚፈቀድና የሚወደድ ይሆናል።

ኢንሻ አላህ ክፍል 2 ይቀጥላል…

*ጣሀ አህመድ (1431ሂ) የተፃፈ*

https://t.me/tahaahmed9
276 views16:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ