Get Mystery Box with random crypto!

Sumeya sultan

የቴሌግራም ቻናል አርማ sumeyasu — Sumeya sultan S
የቴሌግራም ቻናል አርማ sumeyasu — Sumeya sultan
የሰርጥ አድራሻ: @sumeyasu
ምድቦች: ጥቅሶች
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.03K
የሰርጥ መግለጫ

ነጻ ሃሳብ! ነጻ ግጥም!!
ሃሳብ አስተያየት በ @Sumeyaabot አድርሱኝ

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-06-19 19:22:51 ሰላም የ ቻናሌ ቤተሰቦች ከዚህ በፊት እጠቀምበት የነበረው የሃሳብ እና አስተያየት መቀበያ ቦት ተዘግቶ የነበረ ሲሆን አሁን ግን በአዲስ ቦት መጥቻለሁ።
@Sumeyaabot
1.6K views16:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-19 18:26:20 ሱመያ ሱልጣን
"ይህችንም ቀናት በሰዎች መካከል እናዘዋውራታለን"
  ሁሌ ሲከፋኝ እንደማደርገው እሷ ላይ ብሶቴን ልዘረግፍ እየተንደረደርኩ በሯ ላይ ደረስኩ። አይኔን አይታ ይገባታል። እንባዬ ቤተሰብ ከሆነበት ደረቷ ለጥፋ ሰላም አለችኝ። እንደ ሁልጊዜው ጨንቆኝ ስሄድ እንደምታቅፈኝ አይነት፣ ልክ ብትለቀኝ የምበርባት የሚመስል አይነት ጭምቅ የሚያደርግ አስተቃቀፍ። እንደሁልጊዜው ሳልጠየቅ እንባዬን እያዝረከረኩ የሆንኩትን እተርካለሁ።
ለወትሮው አልቅሼ እስኪወጣልኝ በ  ፀጉሮቼ መሃል ጣቶቿን ከትታ እያርመሰመሰች "አይዞሽ፣ ያልፋል፣ አንቺ እኮ ጠንካራ ነሽ..." የመሰሳሉትን ከማለት በዘለለ በለቅሶዬ መሃል ልክ እንደዛሬው ኮስተር ብላ" ምን ሆነሽ ነው?" ብላኝ አታውቅም ነበር። ከደረቷ ስታነሳኝ  እንባ ያበሰበሰውን ሽፋሽፍቴን ገልጬ አየኋት። አሁንም ኮስተር እንዳለች ናት። አጠገቧ ያለውን "ሶፍት" እንድታቀብለኝ ከጀልኩ። "ተነስተሽ ውሰጂ" አለችኝ። ለ አይኔ ተደርቦ ያለቀሰውን አፍንጫዬን በሶፍት አባብዬ መናገር ጀመርኩ። " ዛሬዬ ትላንትናዬ ላይ ሆኜ እንዳሰብኩት አይደለም። ትላንት ላይ ሆኜ ስለ ዛሬ ሳስብ    ከ እንቅልፍ አለመንቃት ብቻ ነበር የሚያሰጋኝ። መንቃት ያጓጓኝ ነበር። ብዙ ህልም ነበረኝ። ግን እንደምታዪኝ ነኝ። በኔ እድሜ ያለ ሰው ቢኖረው የሚያሳዝነኝን አይነት ዛሬ እየኖርኩ ነው። ተስፋ የሌለው ህይወት፣ ከ እንቅልፌም ስነሳ ያው የትላንቱ አይነት ተራ ቀን እንደው ቀየር ካለም የሆነ ተጨማሪ ችግር ቢኖረው ነው። ከጓደኞቼ በታች ነኝ። ነገዬ ላይ ላጣቸው የማልፈልጋቸውን ሰዎች በራሱ ዛሬ ሸሽተውኛል።"ብዙ ማለት ፈልጌ ነበር። ለምን ተሳሰረብኝ?? እንዴት ግን "አይዞሽ "አላለችኝም? ለራሴ ጠይቃለሁ። "ያንቺ ችግር "ከ አላህ ራህመት ተስፋ አትቁረጡ" ከሚለው አንቀፅ የከፋ ነው?? " ችሮታዬ ነገርን ሁሉ ሰፋች" ከሚለው የ ቁርኣን አያት የበዛ ??
ለባሪያው ከ ደምስሩ በላይ ቅርብ ከሆነው ጌታሽ የተሻለ ረዳት ከወዴት ልታገኚ ትከጂያለሽ ሱም??"think about your favourite verse " "ይህችንም ቀናት በሰዎች መካከል እናዘዋውራታለን(3:140) " ለመንጋት ይጨልማል።  ትላንት " አላህ አፊያ ያድርገው" ያልኩትን ሰው " አላህ ይርሃመው" እያልኩ ነው። በፍጹም እንዳታዝኚ አላህ አንቺ ለራስሽ ከምታስቢው በላይ ያስባል፣ አንቺ ራስሽን ከምትወጂው በላይ ይወድሻል። ጌታሽን ከሱ ባለመከጀልሽ እንዳታስቀይሚው"
ልቤ ላይ እርግትትት ሲል ተሰማኝ።
ይህን ቃል አስታወስኩ። *ሱራህ 2, አያህ 186*
وَإِذَا سَأَلَكَ عِبَادِى عَنِّى فَإِنِّى قَرِيبٌ ۖ أُجِيبُ دَعْوَةَ ٱلدَّاعِ إِذَا دَعَانِ ۖ فَلْيَسْتَجِيبُوا۟ لِى وَلْيُؤْمِنُوا۟ بِى لَعَلَّهُمْ يَرْشُدُونَ
ባሮቼም ከእኔ በጠየቁህ ጊዜ (እንዲህ በላቸው)፡- እኔ ቅርብ ነኝ፡፡ የለማኝን ጸሎት በለመነኝ ጊዜ እቀበለዋለሁ፡፡ ስለዚህ ለኔ ይታዘዙ፤ በኔም ይመኑ፤ እነሱ ሊመሩ ይከጀላልና፡፡
================================
@sumeyasu
8.6K views15:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-28 23:20:58           የ እለት ወይዘሮ (ሱመያ ሱልጣን)
ይንጠባጠባል፥ የ ዝናብ ውሃ፥ ከጭንቅላቱ፣
ምን ሻተ ጀሊል? በሱ ላይ ብቻ የማካፋቱ፤
ይገረማሉ፣ ይጠይቃሉ፣
በዙሪያው ያሉ፥ አስሃቦች ሁሉ።
ነቢ ቢሰሙ፥ ስለ ክስተቱ፣
ለ 1 ሸሂድ፥ የሰማይ በሮች፥ የመከፈቱ፤
መልክት ላኩ፥ ወደ ጀሚላ፣
ምን ሰርቶ እንደሆን፥የ 1ሌት ባሏ፤
ትናገራለች፥በሞቱ ዋዜማ፥ ስላገባችው፣
ያ ወጣት ባሏ፥ የፍቅሩን ጣእም፥ ያልተደለችው፤
ባገባት እለት፥ ሌቱን እሷ ዘንድ፣
             ማልዶም ወደ ኡሁድ፤
ጊዜ እንዳጠረው፥ ጀናባ ሊያወርድ።
ለጌታው መሞት፥ እንደናፈቀው፣
በሙሽሪኮች ሰይፍ፥ ዱንያን ራቀው፤
ታጥቦ መምጣቱን፥ ጀሊል ቢሻለት፥
             መላይካ ልኮ፥ ትጥበቱን ሞላው።
"ታውቆኝ ነበር፥ ህልም አልሚያለው፣
ባሌ እንደሚሞት፥ ቀድሜ አውቃለው።
ግን የኔ ምኞት፥ የሸሂድን ልጅ፥ በሆዴ መያዝ፣
               እንደ ሃንዘላ፥ጀግና ልጅ ማርገዝ።"
ትናገራለች፥ በሰርግ ማግስት፥ኢዳ ቁጭ ብላ፣
የ እለት ወይዘሮ፣የ ሃንዘላ ውድ፣ እመት ጀሚላ።
አወይ እድልሽ፥ደረጃሽ ቀና፣
ልጁ ከሆድሽ፥ባልሽ ከጀና፤
ሸሂድ ሃንዘላ፥አዲስ ሙሽራ፣
ባገባ ማግስት፥ጀነት ተጠራ።
   @sumeyasu
2.1K views20:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-04 19:47:48 ተረስቶህ ነው?
(ሱመያ ሱልጣን)
ያ ሁሉ ሃዘኔ፥ እንባና ልመና፣
.............በቃ ቀረ መና??
ያሁሉ የኔ ለቅሶ፣
ያ'ዘን ቋቱን ጥሶ፣
የንባዬ ዘለላ ፥ጉንጮቼን አዳርሶ፤
የጠየኩህን ግን፥ ረሳህ ጨርሶ??
እኮ ተማጽኖዬ፥ ከወዴት ደረሰ?
ምድርን ያረጠበው፣ የአይኔ ፍሳሹ፣
የሰማይን ደጃፍ፥ እንዴት አላራሰ?
  ...................ካንተ ያልደረሰ??
እኮ የኔ ጭንቀት፤ የሃዘኔ መብዛት፣
ለውስጥ ቁስለቴ፥ ፈውስን የማጣት፤
ላንተ ምንህም ነው???
ብዬ ያማረርኩት፥ ከ ጸሎቴ በላይ፣
ካንተ የሚቀርበኝ፤ ባጣ አይደለ ምስካይ?
ከሰጠኸኝ በላይ፥ "ጉደለቴ" የተሰማኝ፣
                      እንደው ግን ምን ነካኝ?
እኮ በምን ስሌት፣
የኔ ለኔ ምኞት፣
የኔ ለኔ ማሰብ፣
ካንተ ከአዛኙ የተወዳደረ?
ኧረ እንዴት ደፈረ?
እኮ እንዴት ሲደረግ?
አንተን ለማማረረ፥ ምላሴ ፈቀደ?
ኧረ እንዴት አቀደ?
እና ጌትየዋ......
በእዝነትህ ሚዛን፥ ውለታህ ተቀምጦ፣
የሰጠኸኝ ደፍቷል፥ ከጠየቅኩህ በልጦ።
እሰይ ክበርልኝ!!!!
ልገዛህ ላምልክህ፥ ያ አዚዝ ያ ገፋር፣
ባይገባኝ ነው እንጂ፥ ላንተ ባሪያ መሆን፣
                                   ለኔ በቂ ነበር።
@sumeyasu
            
4.0K views16:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-10-29 11:05:43
መቼ?
(ሱመያ ሱልጣን)
አየሁ ልበል ከፈገግታሽ፡ ተስፋ መቁረጥ፣
ሰማሁ ልበል፡ ከሳቅሽ ውስጥ፣ የሲቃ ምጥ?
ቆይ ቆይ..
ቆይ መቼ ነው ፡በፊትሽ ላይ ፡መስመር ነገር
                                               የተሳለ?
ምን ቀን ነበር፡ ያ ጉልበትሽ ፡ከ አቅሙ የጎደለ?
በየቱ ሌት፡ የራስ ቅልሽ፡ ነጭ ሞላው?
ያንን ዞማ ያንን ጥቁር፡ በምን ፍጥነት አባረረው?
አርጅተሽ ነው?? በቃ ደክሞሽ??
አንቺ እናቴ ፡ለካ ማርጀት፡ ላንቺም አለሽ።
@sumeyasu
3.8K views08:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-10-20 12:00:45 የሸራው ላይ ምስሌ
(ሱመያ ሱልጣን)
ያ የኔ ጎረቤት፣ ያ ምስኪን ሰዓሊ ፣
                     ሸራውን ወጥሮ፣
የበዙ ቀለምን ፣ከስሩ ደርድሮ፤
ይሞነጫጭራል።
ልብን የሚመስል፥ ትንሽዬ አካል፣
                       በጥቁር አቅልሞል።
ወዲያ በዚያ ደግሞ፥ በጫማ ምስል ስር ፣
                                 የወደቀ አእምሮ፣
አቧራ ቀብቶ፡ ከጭቃ ጋር አስሮ ፣
ከእድፍ ከምሮ።
ደግሞ ባንደኛው ጥግ፡ እጆች ይታያሉ፣
የተንጠለጠሉ፤
የሆነ ብልጭልጭ፡ ሊያወርዱ 'ሚመስሉ።
ያ የኔ ጎረቤት፣ ያ ምስኪን ሰዓሊ፣
                            ፈግጎ ይስላል፣
ደግሞ ይኮሳተራል።
ጥያቄዬን እንደታቀፍኩ ፣አስተዋልኩት
ያንን ሙንጭርጭር፣
ለምን ራሴን አየሁት? ቀድምውንስ እዛ ነበር??
ፊቴን ነው እንጂ ያልሳለው፣
ስእሉማ የኔ እኮ ነው።
የ እጆቼን መዳረሻ፡ ያዛን ልቤን አጠቋቆር፣
በብሩሹ ሳለብኝ፣
የአመታት አኗኗሬን፡ በሸራው ላይ ለጠፈብኝ፤
ይፋ አወጣኝ።
ፊቴን ነው እንጂ የቀረው፣
ምስሉማ የኔ እኮ ነው።
@sumeyasu
3.1K views09:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-08-18 16:00:22 ሴትነትን ሴቶቹ ሲጥሉት
"እውነቴን ነው የምልሽ ወንድ ልጅ ቤት ስትቀመጪለት ይንቅሻል። ከ እጁ ስትጠብቂ ከ ጫማው ዝቅ አድርጎ ነው የሚገምትሽ። አንቺ እቤቴን እቤቴን ብለሽ ጠግቦ እንዲያድር ስትንደፋደፊ እሱ ቢሮው ያለችውን በ ሽንኩርት መላጥ ብዛት እጆቿ ያልጠቆረውን፣ ለጂም ጊዜ ስላላት የሰውነት ቅርፇ ያልከዳትን ፣ ከ አስቤዛ ጎደለ አልጎደለ ብላ ለፋሽን መቀያየር የማትሳቀቀን በ አይኑ ያንደፋድፍልሻል። ይሀው እኔ ልሙት! ስንቷ መሰለችሽ ልጄን በራሴው እጅ ስርዓት አስይዤ ላሳድግ ብላ ቤቷ ችሏት በተቀመጠች ባሏን ለ ውጪ የገበረች። ቤተሰብነትን ብቻዋን ትሰራው መስሏት ብቻዋን ቤቴ ቤቴ ስትል እሱ የውጭ ነገር ብቻ እንዲሰማው ያደረገች። እውነቴን ነው የምልሽ ቤት ከመቀመጥ ፏ! ብለሽ ወጥተሽ መንደር ለመንደር መንከልከል ይሻላል።" ትላለች። በአንድ ካፌ ላይ ከኋላዬ ከተቀመጡት 4 ሴቶች አንዷ።
"ልክ ብለሻል። ሴት ልጅ ከ ወንድ እኩል መሆን አለባት መማር ከባሏ አገዛዝ ሊያወጣት ይገባል። ግን ደግሞ እንድትማሪ አይፈልጉም። እናስተምራታለን ብለው በመሃላ ከቤተሰቦቿ ይለያትና በ አመቱ ልጅ አስታቅፎ ቤተሰቦቿን ልትጠይቅ ስትሄድ ታያታለሽ። " የትምህርትሽስ ነገር?"ብለሽ ስትጠይቂያት "አይ አሁንማ እስቲ ልጄ ከፍ ትበል" ትልሻለች። ከፍ እስኪልላት የ አዲስ ልጅ ነገር ሆኖባት እቤት ውስጥ ትቀመጥለታለች። ከዛ በሚቀጥለው በአል ቤታቸው ሌላ አዲስ ሕፃን ተቀላቅላ የ እናትዬዋን የ እስር ጊዜ መርዘሙን ታበስራለች። ወጥቼ ልስራ ያለች እንደሁ "ምን ጎደለሽ? ልጆቹን አሳድጊ!" ብሎ የ ቤቱ ስራ እንደሚቀል ያህል በቀላል ዓረፍተ ነገር ነገሩን ይዘጋዋል። እስቲ ደግሞ ሌላ አንድ ነጋዴ ሂጂ እና "ሚስትህ ጠበቃ ብትሆን ምን ይሰማሃል?" ብለሽ ጠይቂው "ንዝር" ሲለው ትመለከቻለሽ። መበለጥን አይቀበሉማ። እንደ ድሮው እነሱ ብቻ አዛዥ መሆንን ነው የሚሹት"
አለች። የመጀመሪያዋ ተናጋሪ አሟሟቂ።
"አንቺ እሱን ትያለሽ። መማርማ ቅንጦት ነው። ኩሺና ቦታሽ እንደሆነ የሚያስብ ስንት አባወራ በየቤቱ አለ መሰለሽ። ውጪ ላይ ግን እንደ ሴት አክባሪ ራሱን የሚያይ። ምግብ መስራትሽ የ ሴትነት ግዴታሽ እንጂ እንደ ውዴታ የማያይ፤ እንደ እናቱ ቡና እያፈሉ አባወራን መጠበቅ የትዳር ደንብ የሚመስለው፤ ብቻ ወንድነትን በ አባቱ ልክ የሚመዝን፤ ሚስትነትን በ ሃላፊነት ብዛት የሚያጥር። እስቲ ዛሬ ሂጂ እና "ደክሞኝ እራት አልሰራሁም።"በይው። " እኔ ውጪ ደክሞኝ መጥቼ ምናምን የሚል ዜና ያነብልሻል። የሚሰራውን ስራ እንደ ውለታ እንድታመሰግኚው ይዘረዝርልሻል። የ እውነት ግቢ እና ዛሬ ምግብ መስራት እንዳልቻልሽ ንገሪው። እንደውም "ስለደበረኝ" በይው! ወይም ደግሞ "ከፈለግክ ራስህ ስራ!" በይው እና መልሱን ታይዋለሽ።" አለች 3ተኛዋ። ሲመስለኝ ይሄ ሁሉ ምክር "እሺም" "እምቢም" ሳትል ዝም ብላ ለምታዳምጠው ጉደኛቸው ነበር። "እሺ "አለቻቸው መጨረሻ ላይ። ወሬያቸውን እንደዘጉ "የኔ ቆንጆ እጅሽ ግን ለምንድነው የጠቆረው?" ብለው የነሱን ለስላሳ እጅ ከሷ ስራ ያደከመው እጅ ጋር አነጻሰሩት። "ደግሞ ምንድነው? እንደ በፊቱ አትዘንጪም፣ ከኛ ጋር አትዝናኚም፣ ስራም ሆነ ክላስ አትሄጂም" ብለው ቤቴን ብላ የተቀመጠችን ሴት፤የሆነ ሰውዬን ሚስት በነገር ወጉ።
"አሁን ያቺ ሴት ቤት ስትገባ ስራ ላይ የደከመ ባልን ቤት ስታገኘውና እራት ሲጠይቃት የምትመልሰው፤ ልቡ ሲቀየማት፤ በልቧ ባሏ እንደ ድሮ አባወራ እንደሆነ እና ኋላ ቀር እንደሆነ ሲሰማት፤ ቃላት ሲወራወሩ፤ ግጭት ሲነሳ እና " ድሮም ቤቴን ቤቴን ስል..."በሚል ውለታ ስታሸማቅቀው፤ ባል ጠዋት መልካም ውሎ ተመኝቶላት የወጣውን ሚስቱ አካሏን መልሰው ፍቅሩን እዛው ነጥቀውት የሚጨነቀውን መጨነቅ በአይነ ህሊናዬ እየሳልኩት የምጠብቀው ስልክ ተደውሎልኝ ትቻቸው ወጣሁ። ሴትነትን አንስተው ሲያፈርጡ፤ ወርቅ ሊያለብሱት አልማዙን ጠቆርክ ብለው ሲነቅሉ፤ በንፅፅር ራሳቸውን ባነሰ ሚዛን ላይ ሲያቆሙ ታዝቤ ወጣሁ። ለአድማጭየውም ትዳርም እየጸለይሁ።"
@sumeyasu
3.9K views13:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-08-14 10:57:57        ፋቂው(ሱመያ ሱልጣን)
ተንገጫገጭ ልቤ፥ ድከሚ፣ ባትቺ፣
ከወዲም ከወዲያም፣ ውድቀትን ሸምቺ።
ድከሚ ፣ባትቺ ፥ወዲያም ተንከራተች፣
ያቀረብሽው ሃሳብ ፣ከሄድሽበት ይተች።
ተንገጫገጭ ልቤ፥ ድከሚ፣ ባትቺ፣
ከወዲም ከወዲያም፣ ውድቀትን ሸምቺ።
እዚም ያጣጥሉሽ ፣እዚያጋም ያንቅሩሽ፣
ይሆናል ያልሽውን፤ አይሆንም ይበሉሽ።
ተንገጫገጭ ልቤ፥ ድከሚ ፣ባትቺ፣
ከወዲም ከወዲያም፥ ውድቀትን ሸምቺ።
ግዴለሽም ነፍሴ፣ ጥቂት ተንገዳገጅ፣
                     እንዲያውም ውደቂ፣
ይጉዱት አንቺነትን!፣ ቃሉ እስኪወጣሽ፣
አልችልም እስክትይ፤ " 'ችላለሁ እስክትፍቂ።
ፋቂዋ፣
ያን "እችላለሁ"ን ፣ባልችልም ተኪዋ።
ፋቂዋ፤
ያ'መታት ህልምሽን፣ ካፈር ደባልቂዋ ።
ፋቂዋ፤
ለ"እችላለሁ" አቀንቃኝ፣ ያንን ምላስሽን፣
                       አትችልም በይዋ።
ፋቂዋ፤
ብድግ በይና፥ ከቀበሩሽ ሰዎች፥
ኮቴን ተከትለሽ፣
ጥለውሽ ሲሄዱ ፣በይ በራስሽ ተነሽ።
ያኔ ተመልከቺ፣ ራስሽን አቅኚው፣
ከተቀበርሽበት፣ አንገትሽን አውጭው፤
ከቀባሪዎችሽ ፣አንዱንም አታይው፤
ድሮስ መቅበር ፣እንጂ መዳረሻሽማ፣
                          መቼ ሲገዳቸው?!
በይ አሁን ተነሺ!፣ የተጣለብሽን፣
    የቀብሩን አፈር ፣ከላይሽ አራግፊ፤
ከዛ ወደፊት ግፊ!!!!
በይ ግፊ!!!!
ተንገጫገጭ ልቤ፣ ድከሚ፣ ባትቺ፣
ከወዲም ከወዲያም፣ ውድቀትን ሸምቺ፤
ከፍታ ለመውጣት፣ ከታች ሆነሽ ቧጥጪ።
@sumeyasu
3.1K views07:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ