Get Mystery Box with random crypto!

1 ነት ጀምአ

የቴሌግራም ቻናል አርማ stopsadatkmal — 1 ነት ጀምአ 1
የቴሌግራም ቻናል አርማ stopsadatkmal — 1 ነት ጀምአ
የሰርጥ አድራሻ: @stopsadatkmal
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 569
የሰርጥ መግለጫ

🍃 ነብያቺን ﷺ እንዲህ ይላሉ፦ "ከእናንተ መካከል አንዳችሁ መጥፎ ነገርን ሲሰራ ካዬ ያንን ነገር በኃይል ተጠቅሞ ያስቁም ይሄን ማድረግ ካልቻለ በምላሱ ይቃወም ይህንንም ማድረግ ከተሳነው ያንን መጥፎ ነገር በልቡ ይጥላው በልቡ መጥላቱም ሁሉም በተሳነው ጊዜ ማድረጉ የሚወጅብበት የመጨረሻው ትንሹ ግዴታ ነዉ ።

Ratings & Reviews

3.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-07-11 02:28:48 https://t.me/elmuahlisunamiftahuljenah
48 viewsተቂዩዲን, 23:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-11 02:27:28
እኔን ለምኑኝ እቀበሏቹሀለው አልቁርአን
ነብዩ ሰለሏሁ አለይሂ ወሰለም እንዲህ ይላሉ ለአንድ ባርያ ዱአው ተቀባይነት ያገኛል እስካለቾከለ ድረስ ሰሀቦቹም አንቱ የአሏህ መልክተኛ ሆይ መቾከል ምንድነው አሏቸው እሳቸውም እንደዚ እንደዚ ብዬ አድርጌ ነበር ግን አሏህ አልተቀበለኝም ማለቱ ነው አሉ።
ኡለማዎችም እንዲህ ይላሉ
ሀራም ምግብን የበላ አረባ (40) ዱአው ተቀባይነት አያገኝም!
ሀራም ምግብ ማለት ሰርቆ ወይም አጨበርብሮና ያልተፈቀደለትን መብላት ነው
21 viewsተቂዩዲን, 23:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-10 15:12:48 ግድያ በመፅሀፍ ቅዱስ
-=-=-=-=-=-=-=---=-=-

ብዙ ግዜ ክርስቲያን ወገኖች ነብዩ ሙሐመድ (ሰለሏሁ አለይሂ ወሰለም) በአመፀኛና ፀረ እዉነት በሆኑ ሰዎች ላይ የወሰዷቸዉን ተገቢና ምክንያታዊ የሆኑ እርምጃዎችን በመጥቀስ እስልምና ገዳይና አራጅ እንዲሁ የሰዉ መብት የሚነፍግ ሀይማኖት ነዉ በማለት የተሳሳተና የእንቶ ፈንቶ ድምዳሜ ሲሰጡ ይስተዋላል።

ይህን ሲናገሩ ለሰማቸዉ ክርስትና በፈጣሪዉ ባመፀ ሰዉ ላይ ምንም አይነት ምድራዊ ቅጣትና እርምጃ እንደማይወስድ ያስመስላሉ ግን እዉነታዉን ጠጋ ብለን ስናይ እንደ መፅሀፍ ቅዱስ የዘር ጭፍጨፋን የሚያዝና የሰዉ ደም ያለ አግባብ እንዲፈስ የሚያበረታታ መፅሀፍ በምድራችን ላይ የለም።

አረመኔዉ ንጉስ ሂትለር ቢያያቸዉ እንኳ የሚቀናባቸዉ የሆኑ የመፅሀፍ ቅዱስ አንቀፆችን በጥቂቱ ከጥቂት ማብራሪያ ጋር ላስቃኛቹ:-

ሕዝቅኤል 9
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁵ እኔም እየሰማሁ ለሌሎቹ፦ እርሱን ተከትላችሁ በከተማይቱ መካከል እለፉ ግደሉም፤ ዓይናችሁ አይራራ አትዘኑም፤
⁶ ሽማግሌውንና ጐበዙን ቈንጆይቱንም ሕፃናቶቹንና ሴቶቹን ፈጽማችሁ ግደሉ፤ ነገር ግን ምልክቱ ወዳለበት ሰው ሁሉ አትቅረቡ፤ በመቅደሴም ጀምሩ አላቸው። በቤቱም አንጻር ባሉ ሽማግሌዎች ጀመሩ።

ይህንን ከላይ የለጠፍኩላቹን ሁለት የመፅሀፍ ቅዱስ አንቀፅ በመፅሀፍ ቅዱስ ትንቢተ "ሕዝቅኤል" ምእራፍ ዘጠኝ ከ5-6 ታገኙታላቹ እናም አዉደ ንባቡን ወደላይ ወጣ ብላቹ ብታነቡት ይህ ፍርድ የተፈረደባቸዉ ሰዉች ለጌታ ትተዉ ለፀሀይ በመስገዳቸዉ ነዉ ይህን ከተማመንን አሁን ላይ ክርስቲያኖች እንደሚሉት በክርስትና አስተሳሰብ ሰዉ የፈለገዉን የማምለክ መብት የለዉም። ይህን ካደረገ ይገደላል ማለት ነዉ። ይህ መሆኑ ደሞ በዉሸት ክርስትና ሰዉ የፈለገዉን ቢያመልክ እርምጃ አይወስድበትም መብት ሰቶታል በማለት የሰፉትን ድሪቶ አፈር አባቱን አብልቶ ይቀደዋል ማለት ነዉ።

ከዛ በተጨማሪ ደግሞ በነዚህ አንቀፆች ክርስትና ሴቶችንና ለጋ ህፃናትን እዲጨፈጨፉ እንደሚያዝ አይተናል ይህ ደግሞ የግፍ ግፍ ነዉ ምክንያቱም ሴት ልጅ ደካማ ነች እንደወንድ አትታገል ለምን ትገደላለች ህፃናትስ ምን አቅም ኖሯቸዉ ምን ያዉቁና ነዉ የሚገደሉት?

ይህን አይነቱን የሴትና የህፃናት ጅምላ ጭፍጨፋ እስልምና አጥብቆ ይከለክላል።

ሌላ ቦታ ላይ ደግሞ መፅሀፍ ቅዱስ ኤልያስ የሚሉት ነብይ በዉሸት ነብይ ነን የሚሉ ሰዎችን እንዳሳረዳቸዉ ይነግረናል አንቀፁን እንካቹ:-
“ኤልያስም፦ ከበኣል ነቢያት አንድ ሰው እንዳያመልጥ ያዙ አላቸው። ያዙአቸውም ኤልያስም ወደ ቂሶን ወንዝ ወስዶ በዚያ አሳረዳቸው።”
— 1ኛ ነገሥት 18፥40

አንቀፆች አሁንም ልድገምላቹ:-

2 ዜና 13
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁶ የእስራኤልም ልጆች ከይሁዳ ፊት ሸሹ፥ እግዚአብሔርም በእጃቸው አሳልፎ ሰጣቸው።
¹⁷ አብያና ሕዝቡ ታላቅ አመታት መቱአቸው፤ ከእስራኤልም አምስት መቶ ሺህ የተመረጡ ሰዎች ተገድለው ወደቁ።

ሌላ ተጨማሪ አንፅ:-

1ኛ ነገሥት 21
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²⁸ የእግዚአብሔርም ሰው ቀርቦ የእስራኤልን ንጉሥ፦ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ሶርያውያን፦ እግዚአብሔር የተራሮች አምላክ ነው እንጂ የሸለቆ አምላክ አይደለም ብለዋልና ይህን ታላቅ ጭፍራ ሁሉ በእጅህ አሳልፌ እሰጠዋለሁ፥ እኔም እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ታውቃላችሁ አለው።
²⁹ እነዚህም በእነዚያ ትይዩ ሰባት ቀን ያህል ሰፈሩ፤ በሰባተኛውም ቀን ተጋጠሙ፥ የእስራኤልም ልጆች ከሶርያውያን በአንድ ቀን መቶ ሺህ እግረኛ ገደሉ።

አሁን ከላይ በጠቀስኩላቹ "በ2ኛ ዜና 13" ላይ ከ16-17 ባሉት ሁለት አንቀፆች እና "በ1ኛ ነገስት 21 " ላይ ከ28-29 ባሉት አንቀፆች እንድታሰምሩበት የምፈልገዉ ጉዳይ በእግዝአብሄር ትእዛዝ በተደረጉት በጠቀስኳቸዉ ሁለት ጦርነቶች የተገደሉትን ሰዎች ብዛት ነዉ አንቀፆቹን መለስ ብላቹ ካስተዋላቹሀቸዉ በአንደኛዉ ጦርነት ግማሽ ሚሊዮን (500,000) ሰዎች በሁለተኛ ደግሞ መቶ ሺ (100,000) መገደላቸዉን ታያላቹ ይህን ካስተዋላቹ አንድ አንፃራዊ ነገር እንድታነሱና እንድታስተዉሉ እጠይቃለዉ እሱም ነብዩ ሙሀመድ (ሰለሏሁአለይሂ ወሰለም) ተገደዉ እራሳቸዉን ለመከላከል ባደረጓቸዉ ከ10 በላይ ጦርነት ላይ የሞቱት ሰዎች ቁጥር "756" መሆኑን ነዉ ይህ መሆኑ ኢስላም የሰዉ ዉድመት እንዳይፈጠር ምን ያህል እንደሚጠነቀቅ ቁልጭ አድርጎ ያሳያል።

እና ታድያ በሁለት ጦርነት ብቻ ስድስት መቶ ሺ (600,000)ሰዎችን የጨፈጨፈዉ ክርስትና ወይንስ ከ"10" በላይ በሆኑ ጦርነቶች "756" ሰዎች የሞቱበት እስልምና ከሁለቱ ማነኛቸዉ ናቸዉ የሰዉ መዉደም የማያሳስባቸዉና አራጅ???

እንግዲህ ዉድ አንባቢያን ይታያቹ ክርስቲያኖች ይህንን ሁሉ ግፍ አምቀዉ ነዉ ዛሬ ላይ መተዉ ራሱን ለመከላከል ብቻ ሲል ጦርነት ያወጀዉን እስልምናን የሚተቹት "የራሷ አሮባት የሰዉ ታማስላለች ይለሀል ይህ ነዉ።


ኢብኑ አብራር

ቻናላችንን ለመቀላቀል

https://t.me/joinchat/YlCprY3U05wzNWY8
52 viewsIbnu Abrar አልጋዚ, 12:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-09 16:24:21
እንኳን ለ1443 አመተ ሂጅራ ለኢደል አድሀ አረፋ በአል በሰላም አደረሳቹቹ
ኩሉ አሚን ወአንቱም ቢአልፊ ከይር
93 viewsተቂዩዲን, 13:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-09 11:51:16 ኢየሱስ ገነት አይገባም ..ሲዖል ነው ማረፊያው ይላል መፅሐፍ ቅዱስ ፡፡



https://vm.tiktok.com/ZMNjYJnAr/?k=1

መሰል ስራዎችን ለማግኘት

https://t.me/joinchat/YlCprY3U05wzNWY8
110 viewsIbnu Abrar አልጋዚ, 08:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-06 16:19:39 አስገራሚዉ የመፅሀፍ ቅዱስ ትረካ
-=-=-=-=-=-=-=-=-=-=-=-=-=-=-

መፅሀፍ ቅዱስ በማቲዮስ ምእራፍ "15" አንቀፅ ቁጥር ከ "21" እስከ "28" ድረስ አስገራሚና ቀፋፊ ትእይንቶች ያስቃኘናል ታሪኩን እካቹ:-

ማቴዎስ 15
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²¹ ኢየሱስም ከዚያ ወጥቶ ወደ ጢሮስና ወደ ሲዶና አገር ሄደ።
²² እነሆም፥ ከነናዊት ሴት ከዚያ አገር ወጥታ፦ ጌታ ሆይ፥ የዳዊት ልጅ፥ ማረኝ፤ ልጄን ጋኔን ክፉኛ ይዞአታል ብላ ጮኸች።
²³ እርሱ ግን አንዳች አልመለሰላትም። ደቀ መዛሙርቱም ቀርበው፦ በኋላችን ትጮኻለችና አሰናብታት እያሉ ለመኑት።
²⁴ እርሱም መልሶ፦ ከእስራኤል ቤት ለጠፉት በጎች በቀር አልተላክሁም አለ።
²⁵ እርስዋ ግን መጥታ፦ ጌታ ሆይ፥ እርዳኝ እያለች ሰገደችለት።
²⁶ እርሱ ግን መልሶ፦ የልጆችን እንጀራ ይዞ ለቡችሎች መጣል አይገባም አለ።
²⁷ እርስዋም፦ አዎን ጌታ ሆይ፤ ቡችሎችም እኮ ከጌቶቻቸው ማዕድ የወደቀውን ፍርፋሪ ይበላሉ አለች።
²⁸ በዚያን ጊዜ ኢየሱስ መልሶ፦ አንቺ ሴት፥ እምነትሽ ታላቅ ነው፤ እንደወደድሽ ይሁንልሽ አላት። ልጅዋም ከዚያች ሰዓት ጀምሮ ዳነች።

ታሪኩን እንዳነበባቹት በመጀመሪያ ከነናዊቷ (ከነአናዊቷ) ሴትዮ እየሱስን በአንቀፅ "22" ላይ ልጇን እንዲያድንላት እርር ብላ ጮሀ እንደለመነችዉ ያስረዳናል

ከዛ ወረድ ብለን አንቀፅ "23"ን አስተዉለን ስናነበዉ አሁን ላይ ክርስቲያኖች አዛኝ የሚሉት እየሱስ እንደዛ እየጮኸች የምትለምነዉን #ከነናዊት ሴት ያለ አንዳች ሀዘን ምንም ሳይመልስላት ፀጥ እንዳላትና ደቀ መዛሙርቶቹ ደግሞ <<አረ አንተ ሰዉ እዘን>> የሚሉት በሚመስል ሁኔታ ሴትየዋን እንዲያስተናግዳት ሲለምኑት እናያለን

ወደ አንቀፅ "24" ወረድ ስንል ደግሞ እየሱስ ደቀ መዛሙርቶቹ ቀርበዉ #ከነናዊቷን ሴትዮ የጠየቀችዉን እሺ ብሎ እንዲያሰናብታት ለጠየቁት ጥያቄ <<ከእስራኤል ቤት ለጠፉት በጎች በቀር አልተላኩም>> ብሎ በመመለስ እርሱ የተላከዉ ለእስራኤሎች ነዉና ሴትየዋ ደግሞ እስራኤላዊ ሳትሆ #ከነናዉ ስለሆነች ስለሷ እንደማይመለከተዉ ያስረዳቸዋል

በአንቀፅ "25" ደግሞ ሴትየዋ ልመናዋን አጡፋዉ ሰግዳ ተደፍታ ለመነችዉ

ከዚያም በአንቀፅ "26" እየሱስ እንዲ እርር ብላ ለምትለምነዉ #ለከነናዊቷ ሴትዮ ጥንብ የሆነዉ ዘረኝነት የተጠናወተዉ ለጆሮ የመከብድ አፀያፊ ንግግር እዲህ በማለት ተናገራት ተናገራት:- "የልጆችን እንጀራ ይዞ ለቡችሎች መጣል አይገባም" እንግዴ እዚህችጋ በአዉደ ንባቡ በግልስ እንደምንረዳዉ እየሱስ የራሱን ዘሮች እስራኤላዊያንን "ልጆች" ብሎ ጠርቶ ከነሱ ዉጪ የሆኑት "ቡችላ" እያለ ነዉ ይህ ደግሞ ንፁህ አእምሮ ላለዉ ሰዉ ግልፅና መራር የሆነ ዘረኝነት ነዉ።

ወደ አንቀፅ "27" ወረድ ስንል ደግሞ ሴትየዋ እንዲህ በማለት ለመነችዉ:- አዎን ጌታ ሆይ፤ ቡችሎችም እኮ ከጌቶቻቸው ማዕድ የወደቀውን ፍርፋሪ ይበላሉ” የችግሯን ብችላ የሚለዉ መጠሪያዋን ተቀብላ ነገርግን ቡችላ ከቤቱ አባቶች የወዳደቀዉን ፍርፋሪ እንደሚበላ አስረድታ ፍርፋሪ ይገባኛል ስትል ለመነችዉ

በአንቀፅ"28" ደግሞ እንደ ክርስቲያኖች እምነት የአለማት ጌታ የተባለዉ እየሱስ ይዞት ከነበረዉ አላድንሽም የሚል የተሳሳተ አቋም በአንዲት ተራ ሴት ተሸንፎ ልጇን እንዳዳነላት ይነግረናል

ማጠቃለያ:-
""" """" ""
እንግዲ እንዳያቹት ከማቲዎስ "22" አንስቶ እስከ "28" አንድ አምላክ ከሚባል አካል የማይጠበቁ ቡዙ ነገሮችን አይተናል

◆ለምሳሌ አያዝንም ይህንንም ሴትየዋ እሪይ ብላ ስትጮህ ሰዉ መቶ እስኪለምነዉ ፀጥ በማለት አሳይቶናል።

እና የማያዝንን አካል ጌታ ብላቹ የምታመልኩት ምን ዋስትና አግኝታቹ ነዉ?

◆ለላዉ ደግሞ ዘረኛ ነዉ እሱንም የራሱን ዘሮች ልጆ ብሎ ጠርቶ ሌሎቹን ዘሮች ደግሞ ቡችላ በማለት አሳይቶናል

እና ክርስቲያኖች ሆይ የራሱን ዘር እስራኤሎችን ልጆች ብሎ እናንተን ቡችላ እያለ የሚያዋርዳቹን እንዴት ጌታ ብላቹ ታመልካላቹ?

◆እንደገና ደግሞ እየሱስ እንሚሳሳትም አይተናል እሱንም ሴትየዋን አላድንም ብሎ ሲከራከር ቆይቶ ኋላ ላይ በመልስ ምቷ ተረቶ #ፍርፋራ እንደሚገባት አምኗል እንግዲ አስቡት ይህቺ ሴትዮ እንዲ ባትከራከረዉ ከእስራኤል ዉጪ ላሉቱ ዜጎች የመልእክቴ ፍርፋሪ እንኳ አይገባቸዉም ብሎ ተሳስቶ ይኖር ነበር በዚ አይነት
ማን ያዉቃል አልተከራከሩትም እንጂ አሁንም ስንት የተሳሳተባቸዉ ነገሮች ይኖራሉ

ክርስቲያኖች ሆይ እንዴት የሚሳሳትን ጌታ ታመልካላቹ የሚሳሳት ከሆነ የገነት የሆንከዉን ተሳስቶ ወደ ሲኦልምኮ ሊነዳህ ይችላል ምን ዋስትና ይዘህ ነዉ?

◆ሌላዉና የመጨረሻዉ ደግሞ ከእስራኤል ዉጭ ያላቹ የእየሱስ አማኞች ቡችላ እንደመሆናቹም መጠን የእየሱስ መልእክት ለናንተ አይደለም ምናልባት ከመልእክቱ ባለቤቶች ከእስራኤላዉያን የወዳደቀዉን ፍርፋሪ ካልሆነ በቀር

እኔ የምላቹ ለናንተ የማይገባ ቦታ ሄዳቹ ፍርፋሪ ከምትለቃቅሙ ለአለም ህዝብ ሁሉ ዘር ሳይለይ ተገቢ የሆነዉን እስልምናን ተቀብላቹ ሰላም ለምን አትሆኑም?

ኢብኑ አብራር

ቻናላችንን ለመቀላቀል

https://t.me/joinchat/YlCprY3U05wzNWY8
138 viewsIbnu Abrar አልጋዚ, 13:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-02 01:04:25
138 viewsተቂዩዲን, 22:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-02 00:59:28 https://t.me/elmuahlisunamiftahuljenah
268 viewsተቂዩዲን, 21:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-02 00:59:20 ባጢል ወይም ሀሰት ተከታዩቹ ቢበዙም ሀቅ መሆን አይችልም
ሀቅም ተከታዮቹ ቢያንሱም ሀሰት ሊሆን አይችልም
166 viewsተቂዩዲን, 21:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-02 00:59:20
81 viewsተቂዩዲን, 21:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ