Get Mystery Box with random crypto!

የአማራ ድምጽ

የቴሌግራም ቻናል አርማ stioameamharaspeople — የአማራ ድምጽ
የቴሌግራም ቻናል አርማ stioameamharaspeople — የአማራ ድምጽ
የሰርጥ አድራሻ: @stioameamharaspeople
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 946
የሰርጥ መግለጫ

እውነትን ይዘን ወደ ፊት ✍️

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2023-04-14 03:24:01
Alemu Banta ይባላል። ከወልደያ ጋይንት በጉዞ ላይ እያለ የትምህርት ማስረጃውን ረስቶ ወርዷል። ያገኛችሁ ተባበሩት!
Alex Alex Alex
137 viewsትክክለኛውን መንገድ ምረጥ, 00:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-13 22:19:50
መንግስታዊ Genocide
https://t.me/stioameamharaspeople
196 viewsትክክለኛውን መንገድ ምረጥ, 19:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-13 22:06:23
ለአማራ ህዝብ ነፃነት እና ሰላም ሲሉ መሰዋእትነት ለከፈሉ #የአማራ_የልዩ_ሃይል አባላት ነፍሳቸውን በአፀዴ ገነት ያቆይልን
እነርሱ ሳይሆኑ የሞቱት ያሁኑ ትውልዶች ነን ምክንያቱም እነርሱ ሃላፊነታቸውን በተገቢ ተወጥተው ውድ ህይወታቸውን ሰጥተውን አልፈዋል ።
ለሃገር እና ለህዝብ የተከፈለ ውድ ዋጋ
እኛ ግን በአለ እዳዎች ነን https://t.me/stioameamharaspeople
193 viewsትክክለኛውን መንገድ ምረጥ, 19:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-13 21:55:04
ህዝቡ ከልዩ ሃይላችን ጎን እድሆን በተደጋጋሚ ጥሪ እየቀረበ ነዉ ።
ለአማራ ህዝብ ሲሉ ህይወታቸውን መሰዋእትነት ለከፈሉ የ ልዩ ሃይል አባላቶቻችን ነፍስ ይማር እንላለን ።
ያለ መሰዋእትነት ድል አይገኝም
186 viewsትክክለኛውን መንገድ ምረጥ, 18:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-13 21:48:33 የአማራ ህዝብ ቀኝ እጂ የሆኑት የፋኖ አባቶች የአማራ ህዝብ ከጎናቸው እንድሆን ጥሪ አቅርበዋል ።
ከወደ ወሎ የሚሰማው አንድ አንድ መረጃ አስደሳች ባይሆንም በማህበራዊ ሚዲያ የተሳሳተ መረጃ ከማሰራጨት እንድንቆጠብ ሁሉ ጥሪ ቀርቧል።
185 viewsትክክለኛውን መንገድ ምረጥ, 18:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-13 21:38:35
የኢትዮጵያ መከላከያ ሃይል እጅ አንሰጥም በሚሉ የአማራ ልዩ ሃይሎች ላይ እርምጃ መውሰድ ጀመረ ።
187 viewsትክክለኛውን መንገድ ምረጥ, 18:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-13 21:36:29 እንግዲህ ወገብን ጠበቅ ማድረግ ነው። ህወሀት እያሟሟቀ ነው። ተንደርድሮ ወደ ማይጠብሪ ለመግባት ከሽሬ አሰፍስፎ እየጠበቀ ነው። በማይጠብሪ ግንባር የነበረው ከ15ሺህ በላይ የአማራ ልዩ ሃይል በኦሮሚያ ብልጽግና ውሳኔ መሰረት ከአከባቢው እንዲነሳ ተደርጎ አብዛኛው ወደተለያዩ አካባቢዎች ተበታትነዋል። ቀድሞውኑ ዓላማውም ይኸው ነበረ። ህወሀት ጥይት ሳያስጮህ ፈንዲሻ እየበተነ ማይጠብሪን በቅርቡ በእጁ እንደሚያስገባ ይጠበቃል። በራያ ያለውም ተመሳሳይ ነው። ዛሬ ''የደቡብ ትግራይ'' ዋና አስተዳዳሪ የአማራ ልዩ ሃይል ከራያ መልቀቁን በገለጹበት መግለጫቸው ቀጣዩ ስራቸው ''በአማራ ልዩ ሃይል የተዘረፉትን ተቋማት ማስተካከል'' ነው በሚል የራያን እጣ ፈንታ ምን እንደሆነ ይፋ አድርገዋል።

የብልጽግና ሚዲያዎች አሁንም አሳሳችና ቅጥፈት የተሞላበት ፕሮፖጋንዳዎችን እያሰራጩ ነው። ህዝቡን ያስበሉት የአማራ ክልል አመራሮች በቴሌቪዥን መስኮት ብቅ እያሉ ለኦሮሚያ ብልጽግና አለቆቻቸው ያላቸውን ታማኝነት እስከቀራኒዮ እንደሚደርስ በመግለጽ ላይ ናቸው። የህዝብን ፍላጎት በዚህ መልኩ ማፈን አይቻልም። በጉዳዩ ላይ ያነጋገርኳቸው የአማራ ክልል የአንድ ቢሮ ሃላፊ '' የወልቃይትና የራያ ጉዳይ የህዝብ ነው። ልዩ ሃይል በመኖሩ የተጀመረ ንቅናቄ አይደለም። ወደፊትም ከህዝብ ጋር የሚኖር አጀንዳ ነው። ህዝቡ ወስኗል። በሃይል የሚደረግ ነገር ካለ መጨረሻውን አብረን እናያለን'' ብለውኛል። እኔም በዚህ አምናለሁ። የኦሮሚያ ብልጽግና አይኑን ጨፍኖ የመጠቅለልና የመሰልቀጥ ህልሙን ከዳር ለማድረስ የመጨረሻ ምዕራፍ ላይ እየደረስኩ ነው የሚል መልዕክት በእጅ አዙር እያስተላለፈ ይመስላል። ሁሉንም ጊዜ የሚያሳየን ይሆናል።

አንድ የኦሮሚያ ብልጽግና ዲፕሎማት እዚህ ዋሽንግተን ዲሲ ላይ በአንድ የወዳጃሞች ድግስ ላይ እንዲህ አሉ '' ህወሀትን ጥርሱን አራግፈነዋል። ከእንግዲህ ለእኛ ፈጽሞ ስጋት አይሆንም። አንድ ዙር ጦርነት ከአማራው ጋር ይቀረናል። ከዚያ በኋላ በማዕከላዊው መንግስት ለረጅም ጊዜ በስልጣን ለመቆየት የሚያስችለውን ማረጋገጫ እናገኛለን።'' እንግዲህ ሁሉንም ወደፊት የምናየው ይሆናል። ሌሎች ክልሎችም ልዩ ሃይላቸውን እየፈቱ ነው የሚለውን ደረቅ ፕሮፖጋንዳ እየተጋተ ያለው የኢትዮጵያ ህዝብ ነገሮችን በትዕግስትና በጥሞና እየተከታተለው እንዳለ ተስፋ አደርጋለሁ። መልካም የፋሲካ በዓል!
187 viewsትክክለኛውን መንገድ ምረጥ, 18:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-13 21:32:32 ሱዳን
ሱዳን በሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ላይ ከፍተኛ ግፍ እና ስቃይ እየደረሰ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ ።

in box #ከሻ
በከሻ ጉዳይ ከሚመለከታቸው ከፍተኛ አከላት መረጃ ለማግኘት ሙከራ አድርጌ ነበር።

ያገኘሁት መረጃ ነገር ቢኖር የተጀመረው ከሻ እንዲቆም የተደረገ ነገር ለግዜው እንደሌለ ነው።

እየተካሄደ ያለው ከሻ እንደሚወራው ሀበሾችን ብቻ ላይ ያተኮረ ከሻ አይደለም ማንኛውም ህጋዊ የስራና የመኖሪያ ፍቃድ የሌለው በሱዳን የሚኖር የውጭ ዜጋ የሚመለከት ነው።

ሌላው በከሻ ተይዘው የቅጣት ክፍያ ከፍለው ድጋሚ ቢያዙስ ይቀጣሉ ወይ ብየ ላቀረብኩት ጥያቄ ያገኘሁት መልስም።

በከሻ ተይዘው በፍርድ-ቤት ቀራማ የተቀጡ ሰዎች እኔ እስከማውቀው ድጋሚ እየቀጣን አይደለም ።
አንድ ሰው በአመት ሁለት ግዜ የምንቀጣው ከየት አምጥቶስ ይከፍላል? በከሻ የተቀጡ ሰዎች ቅጣቱን የከፈሉበትን ደረሰኝ ከእጃቸው መለየት የለበትም።
182 viewsትክክለኛውን መንገድ ምረጥ, 18:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-13 16:27:58
214 viewsትክክለኛውን መንገድ ምረጥ, 13:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-13 16:27:53 ህወሓት ለኮረምና አላማጣ አመራር በመመደብ ላይ ነው ተባለ
በኮረም የነበሩ የአማራ ልዩ ኃይሎች ጠቅለው መውጣታቸውን እንዲሁም የፋኖን መበተን ተከትሎ ህወሓት ለኮረምና አላማጣ አመራር በመመደብ ላይ ነው ሲሉ በሥፍራው ያሉ ነዋሪዎች ለአዲስ ማለዳ ገለጹ፡፡

በዚህም ህብረተሰቡ ተረብሿል ያሉት ነዋሪዎቹ፤ “የመከላከያ ሠራዊት እኛ አለን ተረጋጉ እያለ ቢሆንም፣ መንግሥት እያደረገ ያለው እና በህወሓት በኩል እየተወራ ያለው የተናበበ ስለሆነ ህዝቡ ማመን አልቻለም።” ብለዋል፡፡

ህወሓት “የአማራ ልዩ ኃይል ከኮረምና አላማጣ ከወጣ እና ፋኖ ከተበተነ መከላከያ ቦታውን ተረክቦ ቆይቶ ለትግራይ ክልል ይመልሳል” ሲል ነው የከረመው ያሉት ነዋሪዎች፤ “የፌደራል መንግሥቱም ይህን እያስፈጸመ እንዳለ ነው የምናምነው።” በማለት ያላቸውን ከፍተኛ ስጋት ገልጸዋል፡፡

መንግሥት ኮረምና አላማጣን ለህወሓት አሳልፎ ለመስጠት በእርግጠኝነት እኛ የማናውቀው ሴራ እየሰራ እንደሆነ ነው የምናምነውም ብለዋል፡፡

ነዋሪዎቹ ለገበያ ከሚመጡ የማይጨው ነዋሪዎች እንዲሁም እየደወሉ አመራርና ፖሊስ ተመድቦልናል በቅርቡ ወደ ቦታችሁ ትሄዳላችሁ ተብለናል ከሚሉ ሰዎች አረጋግጠናል ባሉት መሰረት፤ ህወሓት በአማጣና ኮረም ለሚገኙ ወረዳዎች በሙሉ ካቢኔ አዋቅሮና ፖሊስ መድቦ ጨርሷል ብለዋል፡፡

ኮረም የነበሩ የአማራ ልዩ ኃይል አባላት ትናንት ጠቅልለው መውጣታቸውን ጠቁመው፤ አላማጣ ውስጥ ያሉት የአማራ ልዩ ኃይልም በጥቂት ቀናት ውስጥ ይወጣል ነው ያሉት፡፡

ወልድያ ከተማ የሚገኙ የአማራ ልዩ ኃይል አባላትም ወደ መከላከያ ሠራዊት አልያም ወደ ፌደራል ፖሊስ ወይም ደግሞ ወደ ክልል ፖሊስ ለመግባት ፎርም እንዲሞሉ እየተደረገ ይገኛል፡፡
አዲስ ማለዳ https://t.me/stioameamharaspeople
219 viewsትክክለኛውን መንገድ ምረጥ, edited  13:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ