ከጊዮርጊስ ጎን መሆናችንን የምናሳይበት ታሪካዊ አጋጣሚ!
በባህርዳር ኢንተርናሽናል ስታዲየም ተገኝተው ቅዱስ ጊዮርጊስ ከሱዳኑ አልሂላል የሚያደርገውን ጨዋታ በሜዳ ተገኝተው መደገፍ ባይችሉ ክለቦን በዚ መልክ ለማገዝ ግን ምቹ ሁኔታ ተፈጥሯል ።
"ባለሜዳ ነን ፥ ባለሜዳ ከመሆን ጥቅሞች አንዱ ደግሞ የስቴድየም ገቢ ማግኘት ነው፡፡ስለዚህም በእለቱ በቦታው ተገኝቼ ክለቤን ባልደግፍም ክለቤ ማግኘት ያለበትን የሜዳ ገቢ እንዲያገኝ የመግቢያ ትኬቱን ግን እገዛለሁ"፡፡ በሚል ሀሳብ ተነስተው ከነገ ነሐሴ 23 , 2014 ዓ.ም ጀምሮ ከዳሽን ባንክ እና በቴሌግራም@AmoleDashenBot!! በመግዛት አጋርነታቸውን ያሳያሉ።
የትኬት ዋጋ ዝርዝር
1 ደረጃ 1,000 ብር
2 ደረጃ 500 ብር
3 ደረጃ 200 ብር
4 ደረጃ 100 ብር
ትኬቶቹ ለእስቴዲየም መግቢያ አያገለግሉም
አንድ ሰው የፈለገውን ያህል መጠን መግዛት ይችላል
በድርጅትም ሆነ በቤተሰብ መግዛት ይቻላል
ከጊዮርጊስ ጎን መሆናችንን ዛሬም በተግባር እናረጋግጥ
@St_Georgefc
@St_Georgefc
የቅዱስ ጊዮርጊሳውያን ድምፅ
THE VOICE OF ST.GEORGEFANS