Get Mystery Box with random crypto!

ኡመተ ረሱል

የቴሌግራም ቻናል አርማ smithhk — ኡመተ ረሱል
የቴሌግራም ቻናል አርማ smithhk — ኡመተ ረሱል
የሰርጥ አድራሻ: @smithhk
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.35K
የሰርጥ መግለጫ

የአላህ ሰላም እና እዝነት በናንተ ላይ ይውረድ ውድ የአላህ ባሮች
በዚህ #channel ላይ የተለያዩ
♥ ኢስላማዊ አስተምህሮቶች
♥ አስተማሪ ታሪኮች
♥ ቀልዶች እና
♥ ወቅታዊ አሳሳቢ ነገሮችን ወደናንተ እናደርሳለን



ለማንኛውም አስተያየት
@Ummate_resul_bot ይጠቀሙ

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-08-31 11:03:23 እንዲህ አይነትም ሰዋዊ ሰይጣኖች አሉና ሰሞኑን ተጠንቀቁ።

«Aselam Aleykum werahmetullahi weberekatu

ትላንት አመሻሽ ላይ ከቤት ሱቅ የተላከች ወጣት መንገድ ላይ መታወቂያ አሳይ ፍተሻ ነው ትባላለች::እንዳልያዘች እና ቤት ነው ስትል ትፈለጊያለሽ ተብላ አንዱ እያዋከበ ነጥሎ ይወስዳታል:: እሷም ወደ ፖሊስ ጣቢያ ሚወስዳት መስሏት ሳታንገራግር ትሄዳለች አሳቻ ቦታ ሲደርሱ ምት ይከተላታል መጨረሻ እራሷን ስታ ስትነቃ በደም ተጨማልቃ ተደፍራ ስውነቷ ቆሳስሎ  ፊቷ አባብጦ በልዞ እሯሷን አገኘችው::

ማታ ተረኛ ሆኜ ማክምበት ሆስፒታል ወላጆቿ ደም እንባ እያነቡ የነገሩኝ አስነዋሪ ድርጊት ነው::
ይህንን ቀውጢ ጊዜ እንደ አጋጣሚ ተጠቅሞ እንዲህ አይነት የእንስሳ ተግባር ሚፈፅሙ የሰው ህሊና የሌላቸው አረመኔዎች አሉና ሁሉም ጥንቃቄ ያድርግ::

አገራችንን ፈጣሪ ሰላም ያድርግልን::»

አንድ ወንድም በውስጥ የላከልኝ መልዕክት ነው። ምን አይነት እንስሳዎች ናቸው በአላህ!


እና ደግሞ መታወቂያ (የቀበሌ፣ መንጃ ፈቃድ፣ ፓስፖርት) እየያዛችሁ ጓዶች!
75 viewsMahiiii , 08:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 22:44:59 https://t.me/fekadu_mag
141 viewsEkram Abdu, 19:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 10:30:32 عن أوس بن أوس رضي الله عنه قال :
سمعت رسول الله ﷺ يقول :

((مَنْ غَسَّلَ يَوْمَ الجُمُعَةِ وَاغْتَسَلَ ، ثُمَّ بَكَّرَ وَابْتَكَرَ ، وَمَشَى وَلَمْ يَرْكَبْ ، وَدَنَا مِنَ الإمَامِ فَاسْتَمَعَ وَلَمْ يَلْغُ ، كَانَ لَهُ بِكُلِّ خُطْوَةٍ عَمَلُ سَنَةٍ أجْرُ صِيَامِهَا وَقِيَامِهَا))

رواه أبو داود.
186 viewsH@ ^^!_! D!, 07:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 10:30:23 عن أوس بن أوس رضي الله عنه قال :
قال النبي ﷺ :

((إنَّ مِنْ أفْضَلِ أيَّامِكُمْ يَوْمَ الجُمُعَةِ فَأكْثِرُوا عَلَيَّ مِنَ الصَّلَاةِ فِيهِ ؛ فَإنَّ صَلَاتَكُمْ مَعْرُوضَةٌ عَلَيَّ))

رواه أبو داود.

«اللَّهُمَّ صَلِّ وَسَلِّمْ عَلَى مُحَمَّدٍ وَعَلَى آلِ مُحَمَّدٍ»
184 viewsH@ ^^!_! D!, 07:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-19 22:28:08 እኚህ ሰው ማን ናቸው?

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

15፥95 *"ተሳላቂዎችን ሁሉ እኛ በቅተንልሃል"*፡፡ إِنَّا كَفَيْنَاكَ الْمُسْتَهْزِئِينَ

ከሊቅ እስከ ደቂቅ፣ ከሕፃን እስከ አዋቂ፣ ወጣትም ሆነ አዛውንት ስለ እሳቸው ሲወራ "ጆሮ ዳባ ልበስ" የሚል የለም። ሁሉ ስለ እሳቸው ሲወራ አዳሜ ሆነ ሔዋኔ ጆሮውን አስግጎ ይሰማል፥ ከሁሉም ከሁሉም የሚገርመው ደግሞ የሚጠሏቸው ሳይቀር እንኳን ቢሆን ስለ እሳቸው ለመስማት እና ስለ እሳቸው ለማወቅ ይፈልጋሉ። ዝም ብለህ ሰው የተሰበሰበበት መሀል ገብተህ እና ድምጽክን ከፍ አድርገህ፦ "እከሌ" ብለህ ወይም "እከሊት" ብለህ ብትጣራ ፊቱን እና ትኩረቱን ወደ አንተ የሚያዞረው የጠራከውን ስም ባለቤት ብቻ ነው፥ ከሌለም ደግሞ ማንም ፊት እና ትኩረት የሚሰጥክ አይኖርም። ነገር ግን ሰው የተሰበሰበበት ስፍራ ሄደህ የእሳቸውን ስም ጠርተህ ንግግር ብትጀምር ሁሉም ፊቱን እና ትኩረቱን ወደ አንተ ያደርጋል፥ ትኩረት የማይሰጥህ የለም ቢባል ማጋነን እና ማበል አይሆንም። ስለ እሳቸው ለማወቅ የማይሰለፍ አይኖርም፥ እኚህ ሰው፦

1ኛ. የእልፍ አእላፋት መጻሕፍት ርእስ በመሆን ብዙ ጸሐፊያን የከተቡላቸው ናቸው፣
2ኛ. በሁሉም ልብ ውስጥ በአሉታዊ ሆነ በአንታዊ በሁለት ወገን እንደተሳለ ሰይፍ ሰርስረው የገቡ ናቸው፣
3ኛ. አስተምህሮታቸው የተሟላ መንፈሳዊ፣ ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፓለቲካዊ የሕይወት ዘይቤ በመሆኑ የዓለማችን ተግዳሮት ነው የተባለላቸው ናቸው፣
4ኛ. "የዓለማችን ቁጥር አንድ አውንታዊ እና አሉታዊ ተጽዕኖ አሳዳሪ" ተብለዋል፥ ለሕሩያን አውንታ ተጽዕኖ እንዲሁ ለእኵያን አሉታዊ ተጽዕኖ አሳዳሪ ናቸው፣
5ኛ. ስለ እርሳቸው ማንነት የገባው ሰው፦ "ሕይወትህን መስዋዕት አርግ" ቢባል ያለ አንዳች ማቅማማት ሕይወቱን እስከ ሞት የሚያደርግላቸው ናቸው።
6ኛ. በታሪክ ውስጥ እሳቸውን ለማነወር፣ ለማበሻቀጥ፣ ለማብጠልጠል ብዙ ጦማሪያን ጦምረዋል፣ ብዙ ኃያሲያን ኃይሰዋል፤ ብዙ ተቺዎች ተችተዋል፣ ብዙ ተሳላቂዎች ተሳልቀዋል። ቅሉ ግን የጦማሪያን ጦማር፣ የኃያሲያን ኂስ፣ የተቺዎች ትችት፣ የተሳላቂዎች ስላቅ ከሟቾች ጋር ሲያልፍ የእሳቸው ስም እና የሰዎችን ሕይወት የቀየሩበት መጽሐፍ እስካሁን አለ የተባለላቸው ናቸው።

እኚህ ሰው ማን ናቸው? አዎ! የዓለማቱ ጌታ የአሏህ መልእክተኛ እና የነቢያት መደምደሚያ ነቢዩ ሙሐመድ"ﷺ" ናቸው። በእርሳቸው ላይ የወረደው ሐቅ ለሰዎች የሚጠቅም ስለሆነ በምድር 1400 ዓመት ቆይቷል፥ ባጢል ቢሆን ኖሮ በእንጭጩ ኮረፋት ሆኖ ተግበስብሶ ይጠፋ ነበር፦
13፥17 *"እንደዚሁ አላህ ለእውነት እና ለውሸት ምሳሌን ያደርጋል። ኮረፋቱማ ግብስብስ ኾኖ ይጠፋል፥ ለሰዎች የሚጠቅመውማ በምድር ላይ ይቆያል፡፡ እንደዚሁ አላህ ምሳሌዎችን ይገልፃል"*፡፡ كَذَٰلِكَ يَضْرِبُ اللَّهُ الْحَقَّ وَالْبَاطِلَ ۚ فَأَمَّا الزَّبَدُ فَيَذْهَبُ جُفَاءً ۖ وَأَمَّا مَا يَنفَعُ النَّاسَ فَيَمْكُثُ فِي الْأَرْضِ ۚ كَذَٰلِكَ يَضْرِبُ اللَّهُ الْأَمْثَالَ
ሐዋ. ሥራ 5፥38-39 አሁንም እላችኋለሁ፦ ከእነዚህ ሰዎች ተለዩ ተዉአቸውም! *ይህ አሳብ ወይም ይህ ሥራ ከሰው እንደ ሆነ ይጠፋልና፥ ከእግዚአብሔር እንደ ሆነ ግን ታጠፉአቸው ዘንድ አይቻላችሁም። በእርግጥ ከእግዚአብሔር ጋር ስትጣሉ ምናልባት እንዳትገኙ"*።

ገማሊያ እንደተናገረው ይህ የነቢያችን"ﷺ" እሳቦት ከሰው ከሆነ ይጠፋ ነበር፥ ግን የነቢያችን"ﷺ" ግልጠተ-መለኮት ከፈጣሪ ስለሆነ ገና በእንጭጭነቱ የመካህ ቁሬይሾች፣ የመዲና በኑ ቁሬይዛህ፣ የሮሙ ባዛንታይን በዕውቀት መሞገት ሲያቅታቸው በጉልበት ሊጠፉት ሞክረው አልተሳካላቸው። ከርሞም ሆነ ዘንድሮም እሳቸው ላይ ለሚሳለቁን ተሳላቂዎች አሏህ በቅቶላቸዋል፥ በእርሳቸው ላይ የወረደውን የአሏህን ብርሃን በአፎቻቸው ለማጥፋት ቢፈልጉ እና ቢጠሉም አሏህ ብርሃኑን ገላጭ ነው፦
15፥95 *"ተሳላቂዎችን ሁሉ እኛ በቅተንልሃል"*፡፡ إِنَّا كَفَيْنَاكَ الْمُسْتَهْزِئِينَ
61፥8 *"የአላህን ብርሃን በአፎቻቸው ሊያጠፉ ይሻሉ፥ ከሓዲዎቹ ቢጠሉም እንኳ አላህ ብርሃኑን ገላጭ ነው"*፡፡ يُرِيدُونَ لِيُطْفِئُوا نُورَ اللَّهِ بِأَفْوَاهِهِمْ وَاللَّهُ مُتِمُّ نُورِهِ وَلَوْ كَرِهَ الْكَافِرُونَ

ይህንን ብርሃን ለማጥፋት እፍ ባሉ ቁጥር እያነደዱት መሆኑን ይዘነጋሉ፥ ኢሥላም በፍጥነት መጠነ-ሰፊ የእድገት መርሓ-ግብር እየታየበት ያለው በምዕራባውያን መሆኑ እፍ ባሉ ቁጥር የሚያነዱበት ውጤት ነው። አሏህ ሂዳያህ ይስጣቸው! ለእኛም ጽናቱን! አሚን።

“ፊዳከ አቢ ወኡሚ ያ ረሡሉሏህ” فِدَاكَ أَبِي وَأُمِّي يَا رَسُول اللَّه

ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
#ሼር
#share #join
Https://t.me/smithhk

ወሠላሙ ዐለይኩም
478 viewsKhalid, 19:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-19 09:05:51 " የአሏህ ሰላም በሙሐመድ እና በመሐመድ ቤተሰብ ላይ ይሁን"
ጁምአ ሙባረክ
347 viewsKhalid, edited  06:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-18 22:29:57 ያ ረሱለላህ! እንወድዎታለን። ይቀበሉናል?

እኛ እርሶን ስንወድ
በእርግጥ የፊትዎን ፍካት ለመመልከት እድል አግኝኝተን አይደለም። ወይም የድምፅዎን መስረቅረቅ በጆሮዎቻችን አዳምጠን አይደለም።

እኛ እርስዎን ስንወድ
ከጎንዎ ሰይፍ አንግተን ከሙሽሪኮች የመፋለም እድል ኖሮን አይደለም። አልያም በኡሑድ ዘመቻ ከእርስዎ ጎን ተሰልፈን ተዋግተንም አይደለም።

እኛ እርስዎን ስንወድ
ቤት ንብረታችንን ትተን በረሀ ለበረሀ ተሰደን አይደለም። እርስዎ ሲሰደዱ ስንቅ አመላልሰንም አይደለም። ወይም እርስዎ ሲሰደዱ ለርሶ መከታ ሆነን ተቀብለንዎትም አይደለም።

ነገር ግን ያ ረሱለላህ! እኛ ወላሂ እንወድዎታለሁ።

ምን እናድርግ! ፍቃዱ የኛ ባልሆነበት ጉዳይ ላይ ከርሶ ዘመን ዘግይተን ተፈጠርን። በወላጆቻችን ላይ አላህ በዋለው የእስልምና ፀጋ እኛም ተቋደስን፤ ስለ እርስዎም እየሰማን አድገን ጎረመስን፤ ስለ እርስዎ እያሰብንም በናፍቆት አነባን።

ዘመንዎን ደርሰን ሳናይ በዘመንዎ የኖርንበት ያህል እየናፈቀን ያልኖርንበትን ዘመን ዳግም በተመለሰ ብለን ተመኘን።

እርስዎ በዘመንዎ ሁነው የኛን ዘመን ናፍቀው እንዳነቡት ሁላ እኛም በዘመናችን ሁነን የእርስዎን ዘመን እየናፈቅን በማንባት የመገናኛ ቀጠሮአችንን በመጠባበቅ ላይ እንገኛለን።
ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም

#ሼር
#share #join
Https://t.me/smithhk
416 viewsKhalid, 19:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-18 22:07:00 የፈረንሳይን ዙፋን ያናወጠችው ሶፊ ፔትሮናን

ፈረንሳዊ ናት በማሊ ሙጃሂዶች ቁጥጥር ስር ውላ ለአራት አመታት መድረሻዋ ሳይታወቅ ከርማለች። አዎ ታግታ ነበር ከተለቀቀች በኋላ ግን የህይወት እስትንፋሷ ወደ ፈረንሳይ ምድር እያምዘገዘገ ጠቅላይ ሚኒስትር ማክሮን ፊት አቆማት። ሊቀበላት ኤርፖርት ድረስ መጣ። ያሳለፈችውን ጊዜ ለመስማት በእጅጉ ጓጓ። በሀገረ ማሊ ስላገቷት ሙጃሂዶች ማንነት ከአንደበቷ ሊያዳምጥ ጆሮውን ቀስሮ ተጠባበቀ።
"አዎ በእርግጥም እነሱ ዘንድ ምርኮኛ ነበርኩ" ብላ ንግግሯን ትጀምራለች

"ለኔ የነበራቸው አያያዝ በአክብሮት የተሞላ ነበር። ምግብ እና መጠጥ ያቀርቡልኛል። ፍላጎቴንም ያሟሉልኛል። ከመሐከላቸው ማንም በቃላትም ሆነ በአካል ትንኮሳ ፈፅሞብኝ አያውቅም። እስልምናን እንድቀበል አላስገደዱኝም። ግና ኢስላምን በሥነ ምግባራቸው ውስጥ አይቼዋለሁ። በአምስት ወቅቶች ወደ ጌታቸው ይዋደቃሉ። ለጌታቸው ያደሩ አልቃሾች። አላህን የሚወዱ ባሮች፣ ለእሱ ኩምሽሽ ብለው የሚያነጉ ፍፁም የጌታቸው ታዛዦች ናቸው .....

አዎ ማክሮን
ሀገራቸው በድህነት የተሞላ ቢሆንም እነርሱ ግን ለሰዎች አዛኝና ተናናሾች ናቸው። የፈረንሳይን ሽቶ አይቀቡም። ነገር ግን ሰውነታችን ንፁህ ልባቸውም ፅዱ ነው። የቅንጦት መኪናዎችን አይነዱም። በረጅም ፎቆች ላይም አይኖሩም። ዓላማቸው ግን ከደመና በላይ፣ እምነታቸውም ከተራራ የጸና ነው" የአንደበቷ አገላለፅ ይጣፍጣል። ንግግሯ ይማርካል። ቀጠለች ...

ማክሮን
"ቁርኣን ሲነበብ ሰምተህ ታውቃለህን? የሚያወሩት ባይገባህም ድምፃቸው ልብን ይሰረስራል። ቀልብህን ያረሰርሳል። ጭንቀትህን ረስተህ አለምን የጨበጥክ ይመስልሀል።
ሴቶቻቸው ጥቁር ኒቃብ ይለብሳሉ። ልባቸው ግን እንደ ወተት ነጭ ነው። ውበት የሌለው ልብሶቻቸው በወንዶቻቸው ዘንድ አያስንቃቸውም። እንደ ጀነቷ እንስት ማታ ማታ ሊያገኟቸው ይጓጉላቸዋል። ከወንዶች ጋር አይቀላቀሉም። ባሏ በሌለበትም ቤቷ ወንድ አይደርስም። አልኮል መጠጥ አይጋቱም። ቁማር አይጫወቱም። ዝሙትም በየጎዳናው አይፈጽሙም።

ከእኛ በላይ የአላህ ነቢይ ኢየሱስንም ይወዱታል ማክሮን ሆይ! ለምን ይመስልሀል?! ሀገራችን በክርስቶስ ስም የንጹሃንን ደም እያፈሰሰች ሀብታቸውን ስለተቀራመተች?! በአገራቸው ሀብት እየቦረቅን ስለክብራቸው ስለተፋለሙ ብቻ አሸባሪዎች እንላቸዋለን።

እነርሱ ግን አለችና .... ሲቃ ተናነቃት እንባዋ በጉንጮቿ በኩል ኩልል ብሎ ፈሰሰ .... "እነርሱ ግን ... እኔም ሆንኩ ሌሎች ታጋቾች በቤተ ክርስቲያን ውስጥ በተማርነው መሰረት እንደ ጭራቅ የተሳሉበትን ገፅታቸውን አላገኘነውም።

ሐዘን ባጠለለው ገፅታዋ እየተመለከተችው
"በመጨረሻም ማክሮን ሌት ተቀን የምትታገለው የልቤን ምት አንቀሳቅሶ ውስጤን በሐሴት የሞላው እስልምና ይህ ነው። ከአሁን በኋላ ፈረንሳይን ውብ አድርጌ አላያትም። አባጣና ጎርባጣዋ የማሊ ገፅታ እኔ ዘንድ የበለጠች ቆንጆ ናት። እንደገና ወደ ማሊ ለመመለስ ወስኛለሁ። በገዛ ፈቃድ ለዘልዓለም ምርኳ ልሆን እሻለሁ። አሁን ግን ቤተሰቦቼንና ዘመዶቼን ወደ እስልምና ልጋብዛቸው መጥቻለሁ። እኔ የቀመስኩትን ጣፋጭ ጣዕም እንዲቀምሱ እፈልጋለሁና።

እናንተንም ከዚህ ታላቅ ሀይማኖት ጋር ያላችሁን ሂሣብ እንድታጤኑት እመክራችኋለው" ንግግሯን ጨረሰች ወሬዋ ውስጤን ሰርስሮት ገብቷል እስልምናን ከፊል ሰዎች ብቻ ለምን ይኖሩታል እኛስ? ስል ራሴን እንድጠይቅ አድርጎኛል። አላህ ይሁነን ወስ-ሰላም።

#ሼር
#share #join
Https://t.me/smithhk
356 viewsKhalid, 19:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-16 22:58:20 ይህ ሁለት ገፅታ ያለው ሰው ማን ነው?!
እጅግ ልብን የሚያደማ የኢራቁ ፕሮፌሰሩ ታሪክ

በተቀዳደደ ልብስና በቆሸሸ ድሪቶ ሰውነቱን ሸፍኖ በኢራቅ ጎዳናዎች ላይ ይዘዋወራል። ግና ምድር ላይ የሚራመድ ሊቅ በሁለት እግሩ የሚጓዝ የአቶሚክ ቦንብ ሳይንቲስትና ፕሮፌሰር ነበር።

ኢራቃውያን ተማሪዎች የከበዳቸው የትምህርት ዘርፍ ሲኖር ወደ እሱ በማቅናት ይጠይቁታል። እሱም አስፓልት ዳር በጣቱ ሲጋራውን ይዞ ፀጉሩን እየፈተለ ፈትፍቶ ያስረዳቸዋል። ዶክተር ሃሚድ ኸለፍ አል-ኦካይሊ ይሰኛል። ትውልደ ኢራቃዊ ነው። በኮምፕሌክስ አቶሚክ ቦንብ ዶክተር በኒውክለር ኬሚስትሪም ፕሮፌሰር ነው።

የካምብሪጅ ብሪቲሽ ዩኒቨርሲቲ ሌክቸሩ ሃሚድ የቆሸሸውን ልብሱን አጥልቆ ረዥም ፀጉሩ ከመሬት አፈር ጋር ተለውሶ ለሚመለከተው ሁሉ በእጅጉ አግራሞትን ይጭራል። አዋቂው እብድም ይሉታል።

ዕድሜ ለአሜሪካ!
ሙሉ ቤተሰቦቹን በጅምላ ሲገድሉበት በዓይን በብረቱ ተመልክቷል። ለወሬ ነጋሪነት እንኳ አንድም አላስተረፉለትም። እናት አባቱ ልጆቹ ሚስቱ ፊት ለፊቱ ነበር የወደቁት። ይህን ልብ አድሚ ክስተት እያነባ ሲመለከት ቆይቶ ከህመሙ ጋር እንዲኖር በካቴና ተጠፍሮ ወደ እስር ቤት አቀና።

እስር ቤት መኖርያው ሆነ። ዘወትር ጁሙዐ ከሌሎች ቀናቶች በተለየ ሽንት ቤት መቀመጫ ላይ በአፉ ተገልብጦ እርቃኑን ከብረት ጋር ተጠፍሮ የሽንትና የሰገራ ሽታ በአፍ በአፍንጫው እየተጋተ ያሳልፋል። እንደ እንሰሳ አንገቱ ላይ ሰንሰለት ተደርጎ በተከበረ ፊቱ ይጎተታል። መሬት ላይ የወዳደቁ ቆሻሻዎችን በምላሱ እያፀዳ በርካታ ቀንና ለሊቶችን ለረጅም ሰአት እየቆመ አሳለፈ። ትንሽ ከስቃዩ ፋታ ሲያገኝ በሐሳብ ጭልጥ ብሎ ቤተሰቦቹን ያስታውሳል። እናቱ በአሜሪካ ወታደሮች ተጨፍጭፋ ስትገደል ልጆቹ እግሩ ስር እየተወራጩ ሲያነቡ በወታደሮቹ ከስክስ ጫማ እየተረገጡ ሲደፈጠጡና የጥይት እራት ሲሆኑ ያስታውሳል። አዎ መጥፎ ትውስታውና ቶርቸሩ ተደራርቦ በደረሰበት ስቃይ የአዕምሮ በሽተኛ ሆነ። ከእስር ቤት ሲወጣ ቤትና ንብረቱ እንኳ አልተረፈ ሁሉም ተዘርፎ ባዶ ቀረ።

አዎ ማንኛውም ሙስሊም በመስቀላዊያኖች እየተሰራች ባለችው በአዲሲቷ የአለም ስርአት ውስጥ ሳይንቲስት የመሆን መብት የለውም።

ሰምተን ዓይናችን ሳያነባ በዝምታ ያለፍናቸው ብዙ መሰል ታሪኮች ይኖራሉ። እኛ ብንረሳቸውም አላህ ግን ፈፅሞ የማይረሳቸው በእርግጥም የእርሱ ባሮች አሉ። መገን አላህዬ አቻቻልህኮ።

#ሼር
#share #join
Https://t.me/smithhk
417 viewsKhalid, 19:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ