ትምህርት ሚንስቴር የ2015 ዓ፣ም ትምህርት ዘመን በመላ አገሪቱ ዛሬ እንደሚጀመር አስታውቋል። ሚንስቴሩ ያዘጋጀው አዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ዛሬ በሁሉም የአገሪቱ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ይጀመራል ተብሎ ይጠበቃል። ሚንስቴሩ ሰሞኑን በሰጠው መግለጫ፣ አዲሱ ሥርዓት ትምህርት በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በቀጣዩ ዓመት እንደሚጀመር ያሳወቀ ሲሆን፣ ዘንድሮ ግን ከመላው አገሪቱ በተመረጡ 80 ትምህርት ቤቶች ብቻ በሙከራ ደረጃ እንደሚሰጥ ገልጧል። አዲሱ ሥርዓት ትምህርት ነባሩን የ6 - 2 - 2 - 2 ቀመር በ2 - 6 - 2 - 4 ቀመር የሚተካ ነው። https://t.me/WolaitaTimes 7.9K viewsNatnael Gecho, 04:54