Get Mystery Box with random crypto!

ከዓለም አቀፍ አሸባሪዎች ተቀድቶ በአማራ ላይ የተፈፀመ የሽብር ስልት (ሚስጥራዊው የእነ አህመዲን | Skyline media

ከዓለም አቀፍ አሸባሪዎች ተቀድቶ በአማራ ላይ የተፈፀመ የሽብር ስልት

(ሚስጥራዊው የእነ አህመዲን ጀበል ሽብርን በሚዲያ የደገፉበት ሰነድ)

ከስር የምትመለከቱት የእነ አህመዲን ጀበል ቡድን የዓለም አቀፍ አሸባሪዎችን ሁነኛ የሽብር ፕሮፖጋንዳ ተከትሎ በአማራና በኦርቶዶክስ ላይ ተግባራዊ እያደረገው ያለው ነው። ሰነዱ ከአንድ አመት በፊት የተሰራ ሲሆን ላለፉት ወራት በርካቶችን አሰልጥነው ወደ ተግባር ገብተዋል። ሰሞኑን በጎንደሩም ሆነ ከዛ ቀደም ባሉት የሽብር ተግባራት የሚጠቀሙት ይህን ስልት ነው። ምን አልባት በዚህ ሰነድ ጠላትና ወዳጅ ተብላችሁ የተፈረጃችሁ ግለሰቦች፣ ሚዲያዎች፣ ፓርቲዎች ትኖራላችሁ። ተመልከቱት።

ኢትዮጵያውያን አገራቸውን ለማዳን ከጠላት ጋር በተፋጠጡበት ወቅት እነ አህመዲን ጀበል የሽብር ፕሮፖጋንዳ ስራ ላይ ነበር። በቅርቡ ከገጠሙት የእነ ሙፍቲ መጅሊስ ጀምሮ በርካቶች በጠላትነት ተፈርጀዋል። ከእነ ቴዲ አፍሮ እስከነ ሀሰን ኢንጃሞ በጠላትነት ተፈርጀዋል። እነ አብንና እናት ፓርቲ በጠላትነት ተፈርጀዋል። ነፃነትና እኩልነት ፓርቲ አላማቸውን የሚደግፍ ፓርቲ ተደርጎ ተቀምጧል። አንዳንድ የመንግስት ባለስልጣናት እንቅፋት ይፈጥሩብናል ተብለዋል።

በዋነኛነት ጠላት የተባለው አማራው ነው። በፕሮፖጋንዳ እናሸብር የተባለው አማራውን ነው። የዚህ ፕሮጀክት ዋነኛ ተሳታፊ ሆነው የቀረቡት እነ አህመዲን ጀበል፣ ኢሳቅ እሸቱ፣ አብዱራሂም አህመድ፣ አብዱልጀሊል፣ ኢብራሂም ሙሉሸዋ ወዘተ ናቸው። የመጅሊሱ ከፍተኛ አመራሮች ጠላት ሲባሉ 17 ኮሚቴ ዋነኛው ደጋፊ ነው።

ይህን አላማቸውን ለማሳካት የማጥቃት ፕሮፖጋንዳን መጠቀም ቀዳሚው አጀንዳቸው እንደሆነ አስቀምጠዋል።

በአማራ ላይ የማጥቃት ፕሮፖጋንዳን እንጠቀማለን ብለው ካስቀመጧቸው 18 ስልቶች መካከል ጥቂቶቹ!
~ወጥመድ ውስጥ መክተት
~ማዋረድ
~ ፍርሃት መፍጠር
~ ችግራቸውን ማባባስ
~ማስጨነቅ
~ ጥርጣሬ መዝራት
~አንድነታቸውን መበታተን
~ማደናቀፍ ወዘተ ናቸው

ይህን ሁሉ በአማራ ላይ አድርገውታል። እያደረጉትም ይገኛሉ። ራሳቸው ሽብር ከፈጠሩ በኋላ እየፈፀሙት ያሉት በሙሉ በእነዚህ ሰነዶች የፃፏቸውን ነው። ይህን ሽብር የሚደግፍ ፋይናንስ ከተለያዩ አካላት አግኝተዋል። ይህን አላማ በአማራና በኦርቶዶክስ ላይ እየፈፀመ ነው። ሽብር ነው። ሽብርን በሚዲያ ማስፋፋት ነው። አልቃይዳ ይህንኑ አድርጎታል። ስልቱ ቃል በቃል የተቀዳውም ከአልቃይዳና ከሌሎች አሸባሪዎች ነው።


(የእነዚህን አሸባሪዎች በሕዝብ ላይ ያቀዱት ሕዝብ ይነቃበት ዘንድ ብታጋሩት ይመከራል)