2022-02-26 21:03:56
ወገን ከሥልጣን የተነሱ ወይም የሚቀነሱ አመራሮች መጪውን ጊዜ በግልጽ ሲነግሩህ ‹‹ለምን አሁን ተናገሩ?›› ብለህ በማናናቅ ፈንታ ‹‹ለምን ተባረሩ?›› ብለህ ጠይቅ፡፡
ምክንያቱም ያለንበት ወቅት የአማራን ሕዝብ ማጥፋት የሚሹ ሃይሎች ሥልጣን የያዙበትና የእኒህን ሃይሎች ዙፋን ማስቀጠል የሚሻ ድርጅት የተሸከምንበት በመሆኑ ከአመራርነት የሚያስባርረው ሙሠኞችን መዋጋት እንጂ ሙሥና መብላት ሊሆን አይችልም፡፡ የሕዝብ ተቆርቋሪ እና የወገን ጠባቂ ሆኖ መገኘት ካልሆነ በቀር ሕዝብን ለጥቃት ዳርጎ የቤተሰብን ምቾት ማረጋገጥ ከሹመት የሚያስነሳ አይሆንም፡፡
➔ከበላይ አካል አንድ ትዕዛዝ ሲመጣ ‹‹ታዛዥ ነኝ›› በማለት ፈንታ ‹‹ተቃውሞ አለኝ›› ያልክ ቀን ግን ገሸሽ ትደረጋለህ፡፡
➔የምትመራውን ሕዝብ ለጉዳት የሚዳርግ እቅድ ሲሰጥህ ‹‹ጠቃሚ ነው›› በማለት ፈንታ ‹‹አውዳሚ ነው›› ያልክ ቀን ጥርስ ውስጥ ትገባለህ፡፡
➔የሚሰጥህን ተልዕኮ ያለ ምንም ጥያቄ ተቀብለህ ሕዝብህ ላይ እየጫንክ ከርስህን እና ኪስህን ከመሙላት ይልቅ የኅሊናህ ተገዥ ሆነህ መቃወምና መጠየቅ የጀመርክ እለት ከጎናቸው ፈቀቅ ትደረጋለህ፡፡
ይሄን ስልህ ግን የሚሰናበተው አመራር ሁሉ ጤነኛ ነው እያልኩህ አይደለም፡፡ በተለያዩ የሥልጣን ሽኩቻዎችና በጥቅም ቅራኔዎች የሚባረሩ ብዙ ጥቅመኞችን ጎጠኞች ይኖራሉ፡፡
በብአዴን መዋቅር ውስጥ ከጎጠኝነት በላይ አማራዊ ስሜት፣ ከተላላኪነት ይልቅ እንቢተኝነት፣ ከአድፋጭነት ይልቅ ተሟጋችነት ከሥልጣን ያስባርራል ማለቴ እንጂ…
አማራን ለማጥፋት ከሚሹ አሸባሪዎች ጋር አብረው ሲሠሩ ከተገኙ ቅጥረኞች በላይ ‹‹ፋኖ ይክስም፣ ልዩ ሃይሉ ይዳከም›› የሚል ትዕዛዝ ሲተላለፍ ‹‹አይሆንም›› ብለው የሚቃወሙ አመራሮች በአሽከሮች ፊርማ ይባረራሉ ማለቴ እንጂ…
ከዚህ ባለፈ ደግሞ…
በሥልጣኑ ሲባልግና ሢሞስን ተገኝቶ በጥፋቱ የተባረረ ወይም ደግሞ ከመናኛ ወንበር ላይ የተወረወረ አመራር ባለመታሰሩ አምላኩን እያመሰገነ አርፎ ይቀመጣል እንጂ ደረቱን ነፍቶ ከሥልጣኑ የተነሳበትን ምክንያትና ባንተ ላይ የተደቀነውን ስጋት አይነግርህም፡፡
በተረፈ ለአንድ ቀን ደፈር ብለው ሐቅን የተናገሩና ጠቃሚ ነገር የሠሩ ብሎም በሕዝብ ዘንድ ትንሽ ሥም ያፈሩ ከዙፋኑ ገሸሽ ሲደረጉ….ለመጣ ለሄደው ‹‹እሺ›› እያሉ ሕዝባቸውንና ኅሊናቸውን የሚሸጡት ግን ወንበሩ ላይ ለሽሽ ብለው ታገኛቸዋለህ፡፡
114 views18:03