Get Mystery Box with random crypto!

ትኩረት ለጎንደር ሙስሊሞች ===================== (የጎንደር ሙስሊሞች እስካሁን ድረስ | Hanadi Ahmed Official

ትኩረት ለጎንደር ሙስሊሞች
=====================
(የጎንደር ሙስሊሞች እስካሁን ድረስ መሳሪያ በታጠቀ ፋኖ እገታ ስር ናቸው።)
||
የክልሉ አላማ አረጋግቼዋለሁ ብሎ ሌላ ኃይል ሳይገባበት በህይዎት የተረፉትን ሙስሊሞች መጨረስ ነውን

አሸዋ ት/ቤት አካባቢ፣ 05 አካባቢ፣ ኪዳነ ምህረትና ባታ አካባቢ፣ 18 አካባቢ አሁንም ጽንፈኞች ተደራጅተው ሌሊት ላይ ጥቃት ለማድረስና የተረፏቸውን መስጂዶች ለማቃጠል እየተዘጋጁ ነው።

በአሁኑ ሰዓት ቁጥራቸው በሺህ የሚቆጠሩ ሙስሊሞች በአራት መስጅዶች ውስጥ ስናይፐር እና መትረይስ በታጠቁ ብዛት ያላቸው ፋኖዎች ከበባ እና እገታ ውስጥ ናቸው።
1, አዲስ አለም
2, ቅዳሜ ገበያ
3, እርግብ በር እና
4, ቀበሌ 10 በሚገኘው መስጅደ ሱና ናቸው ። እስከ አሁን አላፈጠሩም! ህይወታቸውም አደጋ ላይ ነው። አሁንም ከተማዋ በፋኖ ቁጥጥር ስር ናት። የክልሉ መንግስት ሁከቱን ተቆጣጥሬዋለሁ ብሎ ያወጣው መግለጫ ውሸት ነው ብለዋል ከዛው ያሉ ሙስሊሞች!

||
t.me/MuradTadesse