የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫ !
የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የፊታችን እሁድ የሚጠናቀቅ ሲሆን ማንችስተር ሲቲ እና ሊቨርፑል የውድድሩ አሸናፊ የመሆን እድል ያላቸው ሲሆን ሊቨርፑል የሊጉን ዋንጫ ማንሳት የሚችለው ከታች በተዘረዘሩት መንገዶች ነው ።
ሊቨርፑል ዎልቨስን አሸንፎ ማንችስተር ሲቲ ከ አስቶን ቪላ ጋር በሚያደርገው ጨዋታ ነጥብ ከጣለ ሊቨርፑል የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግን የሚያሸንፍ ይሆናል ።
ሊቨርፑል ከ ዎልቨስ ጋር ነጥብ ከተጋራ እና ማንችስተር ሲቲ በ አስቶን ቪላ በስድስት ግቦች ልዩነት ከተሸነፈ ሊቨርፑል የሊጉን ዋንጫ እንደሚያነሳ ተገልጿል ።
ማንችስተር ሲቲ በ አስቶን ቪላ 6 - 0 በሆነ ውጤት ከተሸነፈ እና ሊቨርፑል ከ ዎልቨስ ጋር 5 - 5 በሆነ ውጤት ከተለያየ የሊጉ የዋንጫ አሸናፊ በጥሎ ማለፍ ጨዋታ እንደሚለይ ተዘግቧል ።
@SidaamaMediaNetwork
@SidaamaMediaNetwork