" ፖቼቲኒሆ ፒኤስጂን አይለቅም "
ማንችስተር ዩናይትድ ጀርመናዊውን አሰልጣኝ ራልፍ ራኚክን በአልጣኝነት ለመቅጠር መቃረቡን ተከትሎ በክረምት ማውሪሲዮ ፖቸቲኒሆ ወደ ኦልድ ትራትፎርድ እንደሚያቀኑ በሰፊው ሲዘገብ ቆይቷል ።
የ ፒኤስጂ ስፖርቲንግ ዳይሬክተር ሊዮናርዶ " ማውሪሲዮ ፖቼቲኒሆ ክለቡን የመልቀቅ ጥያቄ እንዳላቀረበ እና የትኛውም ክለብ አርጀንቲናዊውን አሰልጣኝ ፈልጎ እንዳልመጣ " ገልፀዋል ።
ሊዮናርዶ አያይዘውም ስለ ዚነዲን ዚዳን ሲናገር " በተጫዋችነቱ እና በአሰልጣኝነቱ ላከናወናቸው ነገሮች ክብር አለን ፤ ከ ፈረንሳዊው አሰልጣኝ ጋር ግንኙነት እንደሌለን ላረጋግጥላችሁ እወዳለው " ሲሉ ተደምጠዋል ።