Get Mystery Box with random crypto!

ዐርብ በአስራ አንድ ሰዓት ክፍል አስራ ስድስት አቡን ሃሌ ሃሌ ሃሌ ሉያ(፫) ንዜኑ (፫) ዘአ | ሥርዓተ ቤተክርስቲያን Tube

ዐርብ በአስራ አንድ ሰዓት
ክፍል አስራ ስድስት
አቡን
ሃሌ ሃሌ ሃሌ ሉያ(፫) ንዜኑ (፫) ዘአምላክነ ኂሩተ ትሕትና ወየውሃተ ዘእንበለ ዐቅም ዬ ዬ ዬ እንዘ ይጼዕልዎ ኢጸዐሎሙ እንዘ ያሐምምዎ ኢተቀየሙ።

በዚህ ሰዓት

"ለከ ሃይል ፣ ኪርያላይሶንና መልክዐ ሕማማት" የለም።

የሰዓቱን ምንባባትም በቅዳሜ ሌሊት ማንበብ ይቻላል።

           ሥርዓተ እግዚኦታ
ካህናቱ ወደ ቤተ መቅደስ ገብተው ሥርዓተ ግንዘትን ይስሩ : ሦስት ካህናትም ሥርዓተ ግንዘቱን በእጃቸው አቅፈው ይያዙት : አንድ ካህን መስቀልና ጽንሐሕ ይዞ በኋላቸው ይከተል : አንድ ዲያቆን ደግሞ መስቀልና መብራት በመያዝ ፊት ለፊት ይምራ : በምዕራብ በኩል ፊታቸውን ወደ ምሥራቅ አዙረው ይቁሙ : ከዚህ በኋላ በአራቱም ማዕዘናት እየዞሩ እግዚኦታ ያድርሱ አደራረሱም ካህናቱና ሕዝቡ በግራና በቀኝ በአራቱም አቅጣጫ በአራት ተመድበው በመቆም:-

በዐቢይ ዜማ አምስት አምስት ጊዜ : በንዑስ ዜማ ባለአምስቱን ዘጠኝ ዘጠኝ ጊዜ : እንደገና በዐቢይ ዜማ አምስት አምስት ጊዜ : በንዑስ ዜማ በእንተ ማርያም ዘጠኝ ዘጠኝ ጊዜ።

ምሕላው ከተፈጸመ በኋላ ካህኑ "አቡነ ዘበሰማያት" ይስጥ : እስከ ትንሣኤ ድረስ የኑዛዜ ጸሎት ስለሌለ ካህኑ ፵፩ ጊዜ ኪርያላይሶን ይበል : ሕዝቡም እንደርሱ ይበሉ።

#ከዚህ_በኋላ_በቅኔ_ማኅሌት_ሁሉም_ይሰብሰቡ_መቋሚያ_ይዘው_በመካከላቸው_ጧፍ_አብርተው_ይያዙ_የዳዊትንና_የነቢያትን_ጸሎት_እየተቀባበሉ_ያንብቡ_አንብበው_ሲጨርሱ_በመካከላቸው_ያለውን_መብራት_በያዙት_መቋሚያ_ያጥፉት_የዲያቢሎስ_ገዢነት_መደምሰስ_ምሳሌ_ነው_ከዚያም_መዘምራን_ንሴብሖን_ይዘምሩ_ካህናትም_ሕዝቡን_በወይራ_ቅጠል_እየጠበጠቡ_እና_ስግደት_እያዘዙ_ወደ_ቤታቸው_ይሸኟቸው።


አዘጋጅ #ዲያቆን ፍቅረ አብ
ከሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ቻናል!!

https://www.youtube.com/channel/UCyyw8be1uLS-PdwVLd-zyKw

#subscribe ያርጉ ይቀላቀሉ እና ይማሩ

@seratebtkrstian   
@seratebtkrstian   
@seratebtkrstian   


     join