Get Mystery Box with random crypto!

ተዘግቶ የቆየው የማዕድን ግልፅነት ጽሕፈት ቤት እንዲከፈት ተጠየቀ። ከአሥር ዓመታት በፊት በማዕ | ሰሌዳ | Seleda

ተዘግቶ የቆየው የማዕድን ግልፅነት ጽሕፈት ቤት እንዲከፈት ተጠየቀ

ከአሥር ዓመታት በፊት በማዕድን ሚኒስቴር ሥር የተቋቋመው የኢትዮጵያ ማዕድን ኢንዱስትሪ ግልፅነት ኢንሼቲቭ ጽሕፈት ቤት መዘጋት ክፍተት እየፈጠረ ነው በማለት የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ድርጅቶች ኅብረት (ኢሰመድኅ) እንዲከፈት ጠይቋል፡፡ ኅብረቱ የማዕድን ቁፋሮና ማውጣት ዘርፍ ላይ ጥናት ካደረገ በኋላ ነው በድጋሚ ፅህፈት ቤቱ እንዲደራጅ የጠየቀው፡፡

የአምራች ኢንዱስትሪዎች ግልጽነት ኢኒሼቲቭ በዓለም አቀፍ ደረጃ የነዳጅ፣ ጋዝና ማዕድን ሀብት መልካም አስተዳደርን የሚያሰፍን እንዲሁም በዘርፉ ውስጥ ያሉትን ዋና ዋና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት የሚንቀሳቀስ ኢኒሼቲቭ መሆኑን ጥናቱ ያመላከተ ሲሆን መንግሥት ይህንን ጽሕፈት ቤት በድጋሚ እንዲያደራጅ እንዲሁም የሲቪል ማኅበራት ተሳትፎ እንዲጨምር ማድረግ እንደሚገባው ኅብረቱ ይፋ ባደረገው ጥናት ተገልጿል፡፡

ኢትዮጵያ የዓለም አቀፉን ኢኒሼቲቭ ከ2007 ዓ.ም. ጀምሮ አብራ በመሆን የተቀላቀለች ሲሆን፣ በኢትዮጵያ ያለውን ብሔራዊ ኢንሺቴቭ ጽሕፈት ቤት የማዕድን አውጪዎችን ተጠያቂነት በማስፈን፣ የማኅበረሰቡን ተጠቃሚነት በማረጋገጥ፣ የማዕድን ሚኒስቴር የኢኒሼቲቩን የማረጋገጫ ሪፖርት በማዘጋጀት የባለድርሻ አካላት ውይይትና መረጃ የማሠራጨት ሥራዎችን ይሠራ እንደነበር ሪፖርተር ፅፏል፡፡