Get Mystery Box with random crypto!

❤ የፍቅር ግጥም🌹

የቴሌግራም ቻናል አርማ selafeker — ❤ የፍቅር ግጥም🌹
የቴሌግራም ቻናል አርማ selafeker — ❤ የፍቅር ግጥም🌹
የሰርጥ አድራሻ: @selafeker
ምድቦች: ስነ-ጽሁፍ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 12.61K
የሰርጥ መግለጫ

🌹 💔 ❤
💊🔮 ከፍቶሀል?🙍‍♂
ከፍቶሻል? 🙍‍♀
🚬 አስደስታችኋል ብዬ ቃል አልገባም😥 ስሜታችሁን ግን እጋራለው💔 እናም ማንም ሰው እንዲያፅናናኝ አልፈልግም 🙅‍♂
ለአድናቆት @Addisu32
Join 👇requests የሚለውን ይጫኑ 👇

Ratings & Reviews

1.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 21

2022-07-11 18:33:38 Here we make money by buying packages and get spins everyday number of spins and benefit of each package are there in presentation https://spin2money.net/7174600035177309?s=tg
2.7K viewsAddisu, 15:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-10 16:07:34 ለመላው ኢትዮጵያዊያን ሙስሊም ወገኖቻችን በሙሉ እንኳን ለ1443'ኛው የዒድ አል አድሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ!

ዒድ ሙባረክ!

@selafeker
@Addisu32
3.5K viewsAddisu, 13:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-05 19:32:28 ​#የከንቲባው_ልጅ

ክፍል 25


በህይወቴ ለመጀመሪያ ጊዜ ሽጉጥ ተደቅኖብኝ እየተዛተብኝ ነው።ከዚህ ለማምለጥ ደግሞ ሰውዬው የሚለኝን ነገር ማድረግ የግድ ነው ። 'እሺ ምንድነው እንዳደርግልህ የምትፈልገው ...?' አልኩት በብስጭት ። "አንድ ነገር ብቻ ነው የማዝህ ፣ እሱም የከንቲባውን ልጅ እኔ ወደ ምልህ ቦታ ይዘሀት ትመጣለህ ። ከዛን ልጅቷን በሰላም ተረካክበን ፣ አንተ ደግሞ በምላሹ ወደ ጫካ ስትገባ የተቀረፅከውን ፣ እንዲሁም የእጅ ሰዓትህና የአንገት ሀብልህን ከነ ህይወትህ ይዘሀቸው ትመለሳለህ ። አለቀ ፤ በቃ ይኸው ነው" አለኝ ቀለል አድርጎ ። የመጀመሪያ ቀን ከህይወት ጋር ስንገናኝ "የከንቲባ ልጅ ነኝ" ብላኝ ስትተዋወቀኝ ያን ቀን በልቤ ለራሴ 'በቃ ተስፍሼ ቁርጥህን አወቅ ፡ ነገ ወይ ከርቸሌ ፡ ወይም ደግሞ ሲኦል ትገባታለህ' ያልኩት ትዝ አለኝ ። 'ቆይ ግን ከሷ ምንድነው የምትፈልገው ...?' ስለው "እሱ ያንተ ጉዳይ አይደለም" አለኝ በሽጉጡ ግንባሬን እየተጫነኝ ። ባይታየኝም ወደላይ ቀና ብዬ እያየሁት 'ቆይ አንተ ማነህ ፡ ለምንስ ነው እንደዚህ የምታደርገው...?' አልኩት በልመና አይነት ድምፅ ። "እኔ ማለት የናንተ ጥቁር ጠባቂ መላክ ነኝ ። በሄዳችሁበት ሁሉ አለው ። ደብረዘይት ብትል ፣ ድሬዳዋ ዩኒቨርስቲ ብትል ፣ ሌላው ይቅር ፣ የከንቲባውን ልጅ ቤት መብራት ማጥፋትና ማብራት እንኳን የኔ ስራ ነው" ሲለኝ ሙሉ ነገር ጭልምልም አለብኝ ። ከዚህ በፊት ሲከታተለን የነበረውና በፍርሃት ስንጠብቀው የነበረው ሰውዬ እንደሆነ ተረዳሁ ። ግን ጥያቄ የሆነብኝ ነገር ነበር ። ህይወትን ከሆነ የሚፈለገው ፡ ለምን ከዚህ በፊት ያገኛቸውን አጋጣሚዎች እንዳልተጠቀመ ጠየኩት ። እሱም "ደብረዘይት ፡ ኩሪፍቱ ሪዞርት ውስጥ ሁሉ ነገር አልመች አለኝ ። ከዛ ስትወጡ ልይዛት አቅጄ ነበር ። ግን እኔ ባላሰብኩበት ቀን ከዛ ለቃችሁ ወጣችሁ ። እዚህ ደግሞ እንዳልይዛት ልጅቷ ከቤት አትወጣም" ። ሲለኝ 'ታድያ ምን ይሳንሀል ፣ መብራቶቹን ያበራኻቸው በፀሎት ነው እንዴ ፣ ልክ ገብተህ እንዳበራኻቸው ልጅቷንም ገብተህ መውሰድ እኮ ትችላለህ' አልኩት ። እሱ ግን ይበልጡኑ በሽጉጡ እየተጫነኝ "ስማ አንተ ወጠጤ ፡ እዚህ ያመጣውክ እንድትመክረኝ አይደለም ። ለመጨረሻ ጊዜ ደግሜ እጠይቅሃለሁ ። ልጅቷን እኔ ወደ ምልህ ቦታ ይዘሀት ትመጣለህ ወይስ እዚሁ ግንባርህን ለሁለት ልክፈልልህ...?" አለኝ እየደነፋብኝ ። በጣም ጨንቆኛል ፤ እሱ ባይተኩስብኝም ጭንቅላቴ አሁን እራሱ ለሁለት ክፍል ብሏል ። አንደኛው 'ተው ተስፋዬ ለማታውቃት ልጅማ እስከ ሞት የሚያደርስ መስዋዕትነት መክፈል የለብህም ። ባይሆን ላንተ ሲሉ ቀን ከሌሊት የሚለፉ ቤተሰቦችህን አስባቸው ። ደግሞስ እሷ የከንቲባ ልጅ እንጂ ማራኪክ አይደለች' ይለኛል ። ሁለተኛው ደግሞ 'አይዞህ ፡ በርታ በል ፡ ይሄ የህይወት ፣ የህሊናና የሰውነት ጉዳይ ነው ። ልጅቷ ፡ እህትህ ፣ ፍቅረኛህ ፣ እናትህ ወይንም ደግሞ ወደፊት የምትኖርህ ሴት ልጅህ እንደሆነች አስብና የሰውዬውን ጥያቄ ውድቅ አድርግ' ይለኛል ። ሰውዬው በሀይል "አንተን እኮ ነው የማወራው" ብሎኝ ከሀሳቤ አነቃኝ ። ትዕግሥት የሚባል ነገር አልፈጠረበትም ። ቀጠለና #10 second እሰጥሃለሁ ። ካንተ መስማት የምፈልገው 'እሺ' የሚለውን ቃል ብቻ ነው አለኝና መቁጠር ጀመረ ። #10 ፣ #09 ፣ #08 ፣ #07 ፣ #06 ፣ #5 አለና #4 ላይ ሲደርስ ሽጉጡን አቀባብሎ መቁጠሩን ቀጠለ ፣ #03 ፣ #2 ፣ #1 ...

'እሺእእእ ...' አልኩት ቅልጥ ባለ ድምፅ ። የሱ አንድ እና የኔ እሺ ማለት እኩል ከአፋችን ሲወጣ የሽጉጥ ድምፅ ሳይሆን "አንድ ሺ" የሚል ቃል ነበር የተሰማኝ ። በእጆቹ እያጨበጨበ "ጎበዝ ልጅ ፤ ጥሩ ምርጫ ነው" አለኝ የፌዝ ይሁን የደስታ የማላውቀው የሳቅ አይነት እየሳቀ ። ቀጠልኩና 'እሺ ለምን እንዳልኩህ ግን ገብቶሃል ...? ሳታስጨርሰኝ ነው እኮ ማጨብጨብ የጀመርከው' ስለው "ያልኩህን ለመፈፀም ነዋ ፣ ሌላ ለምን ሊሆን ይችላል...?" አለኝ ። እኔም 'አይደለም ፡ አላስጨርስ አልከኝ እንጂ ልልህ የፈለኩት እኮ ፡ እሺ ከምትገለኝ ምናለበት እስር ቤት እንድገባ እንኳን ብትፈቅድልኝ ለማለት ነበር' አልኩት የማላገጥ ሳቅ እየሳኩበት ወኔዬ ከየት እንደመጣ ሳላውቅ ። ወዲያው መልስ ምት ነው መሰለኝ አይቼውም ቀምሼውም የማላውቀውን ጥፊ ድርግም ሲያደርግብኝ ለአስር ሴኮንድ ምድር ጨለመችብኝ ። ቀጥሎም አንገቴን አንቆኝ "ቆይ ማነኝ ነው የምትለው ...? ለልጅቷስ ይሄን ያክል እራስህን ለሞት አሳልፈህ የምትሰጠውስ ለምንድነው ? ልጅቷ ምንህ ነች .?" አለኝ ሀይል በተቀላቀለበት ድምፅ 'ስሟን አታውቅም እንዴ ? ህይወቴ ናት እኮ' አልኩት እንደ ማይገለኝ ስለታወቀኝ ደፋር ሆኜበት የሚለኝን እሺ ካላልኩት የሚገድለኝ ቢሆን ኖሮ መጀመሪያውኑ ወደ ጫካው ስገባ Video መቅረፅ አይጠበቅበትም ነበር video ሊቀርፀኝ የፈለገበት ምክንያትም እሺ ካላልኩት ለማስፈራሪያነት ሊጠቀምበት አስቦ እንደሆነ ግልፅ ነው ይህ ሳይሆን ቀርቶ የሚገድለኝም ከሆነ ግን የጀግና ሞት ልሙት ብዬ እንጂ ለመሞት ዝግጁ ሆኜ እንኳን አይደለም በዚች ምድር ላይ የምንሞትለት ሰው ከሌለ የምንኖርለትም ሰው አይኖርም አለውልሽ የሚለው ቃል ትርጉም የሚያገኘው ስትሞትላትም ጭምር ብቻ ነው በአፍ ብቻ አለውልሽ ከጎንሽ ነኝ ፣ ምንጥሴ ቅብጥርሴ ማለት እራስን ማታለል ነው ለሰው ልጆች ሁሉ መኖር ብቻ ሳይሆን መሞትንም ጭምር ከክርስቶስ ተምሬያለሁ እየሰቀሉት እንኳን "የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው" እያለ ለገዳዮቹ ይፀልይ ነበር እኔ ደግሞ እንደ እርሱ ለጠላቶቼ ጭምር የምሞትበት አቅም ባይኖረኝ እንኳ ፤ ብያንስ ለወዳጆቼ መሞት አይከብደኝም ህይወት ደግሞ ለኔ ከወዳጅም በላይ ናት አይኖቿ እንዴት በስስት እንደሚያዩኝ ፈጣሪ ብቻ ነው የሚያውቀው ወደ ጊቢ ለመመለስ ከቤታቸው ስወጣ እንኳን ፀሀይ የሚመስለው ፊቷ በአንዴ ከለሊቱ ስድስት ሰዓት ይሆናል እርግጠኛ ነኝ በኔ ቦታ ብትሆን ሳታንገራግር ህይወቷን ትሰጠኛለች በዚህም በዚያም ግን እኔ ለሰዎች መሞትን እንጂ ሰዎች እንዲሞቱልኝ አልፈልግም ከጥቂት ደቂቃ በዋላ የቤቱ መብራት ሲበራ አይኖቼ ሰውዬው ላይ ፈጠው ቀሩ ፊቱ አዲስ አልሆነብኝም አይኖቼን ጨፍኜ ለማስታወስ ሞከርኩ አይምሮዬ ይህ የህይወት አባት አይደሉም እንዴ ? ይለኛል አይኖቼን ገልጬ ድጋሜ ትኩር ብዬ ተመለከትኩት አዎ ልክ ነኝ ፤ እራሳቸው ከንቲባው ናቸው ሀሙስ ምሽት እነ ህይወት ቤት ግንባሯን ስሟት ወይናቸውን ይዘው ወደ መኝታ ክፍላቸው ሲሄዱ በትንሹም ቢሆን ፊታቸውን አይቼ ነበር ታድያ ምን እየተካሄደ ነው ? ምንስ ለማድረግ እየሞከሩ ነው ?

✎ ክፍል ሀያ ስድስት ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

ይቀጥላል.....
አሪፍ አሪፍ ግጥም እና ታሪክ ለማግኘት
@selafeker
@selafeker
@Addisu32
5.5K viewsAddisu, 16:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-05 19:26:59

#መስዋዕትነት

ክፍል

"ማለት? በምን ምክንያት ማለቴ እንዴት?...."
"ሌላውን ቀስ ብዬ እነግርሻለው ምክንያት ላልሺው መልሱ አንቺ ነሽ..."

" ማለት ምን እያልከኝ ነዉ ያለኸዉ" አልትኩት ግራ ገብቶኝ አይን አይኑን እያየሁት

ሊያዬ በሽታሽ ላንቺ እንደተነገረሽ ቀላል አልነበረም፡፡ የሆነ ጊዜ ትምህርት ቤት ራስሽን ስተሸ ከደረጃ ላይ እንደወደቅሽ ታስታዉሻለሽ አይደል፡፡ አንገቴን በአወንታ ነቀነኩለት፣ (እንዴት አላስታዉሰዉም ለሁላችንም ከባድ የሰቆቃ ጊዜ ነበረ፡፡ ፡፡ በወደኩ ሰዓት እጄ ወልቆ ያልሄድኩበት ውጌሻ አልነበረም እትዬ ዘይነባ ከሄዱበት ሀገር እስኪመለሱ። እትዬ ዘይነባ የታውቁ የሰፈራችን ወጌሻ ናቸው ውልቃት ይሁን ስብር ዘይነባ ጋር መፍትሄ አለው... ከሳምንት ጭንቅ በኋላ መጡልኝ እና ከነፍስ ውጪ ነፍስ ግቢ ትግል ብኋላ ግጭ አድርገው ወደነበረበት መለሱት.... )

"በዛን ሰዓት ልብሽ ከፍተኛ የሚባለዉ ደረጃ ላይ ደርሶ ስለነበር በሶስት ወር ዉስጥ ሄደሽ ካልታከምሽ እንደምትሞቺ ለቤተሰቦቺሽ ተነገራቸዉ፡፡ መሲም የተፈጠረዉን ሁሉ መጥታ ነገረችን፣ ያላደረግነዉ ነገር አልነበረም መሲ ሻርፕ አንጥፋ እስከመለመን ደርሳ ነበር፤ ግን ተለምኖ እስከሚሰባሰብ አንቺ ልትሞቺ ሆነ፡፡ ሁላችንም ተጨንቀን ባለበት ሰዓት መሲን አባትሽ ደዉሎ ጠራትና አዲስ አበባ ሄደች…"

"ቆይ አንዴ እናንተ ይሄን ያክል ከለፋችሁ እስከማዉቀዉ እነ አባቢም ዝም ብለዉ አልተቀመጡም… እንዴት አምስት መቶ ሺህ ብር ሳይሞላ ቀረ"

"ለህክምና የሚያስፈልግሽ አንቺ የምታዉቂዉ አምስት መቶ ሺህ ብር ሳይሆን 1.2 ሚሊዮን ብር ነበር… "

"ምምምምን... እንዴት ሳይነግሩኝ ማለቴ እኔኮ የማዉቀዉ…"

"ያልነገሩሽ አንቺ እንዳትጨነቂና ተስፋ እንዳትቆርጪባቸዉ ነበር… ብዙ ለፉ የየሰዉን ደጅ አንኳኩ አባትሽ አለኝ የሚሉት ጓደኛቸው አቶ ደምሴ ጋር ሄዱ፤ 'ከዚህ ቀደም እንደነገርኩህ ነው ልጅህን መሰረትን ዳርልኝና ሙሉ ወጪዋን ችዬ አሳክምልሀለሁ' አሏቸው ። ነገሩ ሁሉ ከአቀማቸዉ በላይ ነበር፡፡ እያዩሽ ወደሞት ልትሄጂባቸዉ ሆነ" በረጂሙ ተነፈሰና ከአልጋዉ ተነሳ

"እስኪ የሆነ የሚቀመስ ነገር ካለ ታች እንዉረድ" አለኝ እጄን እየያዘ

"ይሄንን ጉዴን ነግረኸኝ ሳትጨርስ የምን ምግብ በዛ ላይ በዉድቅት ሌሊት..."

"ልክ ነሽ ሊያዬ ግን ራትም አልበላዉም በዛ ላይ አንቺም …" ንግግሩን ሳይጨርስ አቋረጥኩት

"በቃ እሺ እንደዛ ከሆነ ሂድና በልተህ ና እኔ እዚሁ እጠብቅሀለሁ" ምንም ሳይለኝ ወደታች ወረደና ትንሽ ቆይቶ ሁለት የታሸገ ምግብ ይዞ መጣ፡፡ አንዱን ለኔ አቀበለኝና "መጀመሪያ እንብላ ካለዛ አልነግርሺም" አለኝ ፈገግ እያለ በፈገግታዉ ዉስጥ ለኔ ምን ያክል እንደሚያስብልኝ ተረዳዉ፡፡ ፍላጎቱ ባይኖረኝም የሰጠኝን ምግብ ትንሽ በላሁና እሱ እስከሚጨርስ ጠበኩት፡፡

" እሺ ከዛስ" አልኩት እንደጨረሰ

"አማራጭ ሲያጡ የመጨረሻዉን አማራጭ ለመጠቀም ተገደዱ እሱም መሲን ከአባትሽ ጓደኛ ከአቶ ደምሰዉ ጋር ማጋባት እና ብሩን መቀበል"

"እና! መቼም አደርገዉት ነበር አትለኝም…"

" እሱን ልነግርሽ አይደል … ለሁሉም የቀረዉ የመጨረሻ ምርጫ ይህ ነበር፡፡ መሲ ህመምሽ ሳይብስ በፊት ነገሩን ሰምታ ነበር እናም እንደሰማች ከአባትሽ ጋር ከፍተኛ ጥል ዉስጥ ገብተዉ ነበር..(አስታወስኩ የደበቁኝ ሚስጥር ሁሉም ነገር አንድ በአንድ እየተገለፀልኝ መጣ) ለነባም ነግራዉ ነበር፡፡ ምናልባትም ነባ በህይወቷ ዉስጥ ባይኖር ብታጣ ትምህርቷን ማቆም እና የአንድ ሽማግሌ ሰዉዬ ሚስት መሆን ወይም እንደ ሁኔታዉ የማትወደዉን ሽማግሌ አግብታ መማርን ትመርጥ ይሆናል፡፡ የነባ መኖር ግን ህይወቷን ከባድ አደረገባት...
አባትሺም የጠሯት ለዚሁ ጉዳይ ነበር፤ አወሩ እና ዉሳኔያቸዉን ወሰኑ እሱንም አሳወቋት፡፡ 'ከአንድ ወር ከአስራ አምስት ቀን በኋላ ደምሰዉን ታገቢዋለሽ የሰርጋችሁ እለት ብሩን ሊሰጠን ተስማምቷል ከዛ በኋላ ያለዉ ያንቺ ዉሳኔ ነዉ ብቻ እህትሺን አድኛት ይሄ አይሆንም የምትዪና ለሰርጉ ከጎንደር የማትመጪ ከሆነ የኔና ያንቺ አባትና ልጅነት ያበቃለታል፡፡ እህትሺን የቀበርኩ እለት ባትሞቺም በሀሳቤ እቀብርሻለሁ' ቃል በቃል እንደዚህ አሏት መሲ አማራጭ አልነበራትምና ተስማምታ ወደኛ ተመለሰች ግን በድኗ ነበር የተመለሰዉ ወር ሙሉ ጠጣች… ጠጣች… ጠጣች… ብዙ ሰከረች ነባም ተባባሪዋ ሆነ ይጠጣሉ የሆነ ቦታ አልጋ ይዘዉ ያድራሉ፡፡ ታዲያ በዚህ መሀል ያለጥንቃቄ ወሲብ እንደሚያደርጉ እኳን ማስተዋል አቅቷቸዉ ነበር፡፡

የሆነ ቀን አብረን ምሳ እየበላን መሲ ልትጎርሰዉ ያለቺዉን ምግብ እንዳንከረፈፈች በሀሳብ ሄደች እያየኋት ነበር፤ እጇ ላይ ያለዉን ምግብ ጣለቺዉና ወደ ነባ አፈጠጠች አሱም ግራ ተጋብቶ አያት… ተነስታ እጁን እየጎተተች ይዛዉ ወጣች ትንሽ ቆይተዉ ተያየዘዉ ተመለሱ 'ምን ተፈጥሮ ነዉ መሲ ሰላም አይደለም' አልኳቸዉ፡፡ 'ባክህ መሲ ሳታረግዝ አትቀር…'
ተናግሮ ሳይጨርስ አቋረጠችዉ 'አንተ ባልተረጋገጠ ነገር እንደዚህ አትበል ገና መች አወቅን' እንደዛ ከሆነ ተነሱ ሀኪም ቤት እንሂድ ብዬ ተያይዘን ወጣን… ምርመራ ተደረገላት እዉነት ነበር መሲ የሶስት ሳምንት ነብሰ ጡር ናት...

ይቀጥላል....
አሪፍ አሪፍ ግጥም እና ታሪክ ለማግኘት
@Addisu32
@selafeker
@selafeker
4.3K viewsAddisu, 16:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-02 23:03:50
5.2K viewsAddisu, 20:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-01 07:45:45 ​#የከንቲባው_ልጅ

ክፍል 24

ድሬዳዋ ግን UNESCO ላይ አልተመዘገበችም ...? ማለቴ ባላት በቂና አስተማማኝ የአዋራ ክምችት መመዝገብ ያለባት ይመስለኛል ። (#10 09 2011) ከእንቅልፋችን ስንነቃ ያየነውን ግን እንኳን ዩኔስኮ ፡ ቅዱስ ገብርኤል እራሱ በህይወት መፃፍ ላይ ይከትበዋል ። (የከተሜ ልጆች ፡ ይከትበዋል የምትለዋ ቃል ደግሞ ክትባት እንዳት መስላችሁ ...) ። ተቀርፆ አለም ሁሉ በቲቪ ቢያየው ደስ ይለኝ ነበር ። anyways እኛ በስልክም ቢሆን ቀርፀናል ። በህይወቴ ለመጀመሪያ ጊዜ ተፈጥሮ ሲቀየር አየሁ ። አዋራ እንደ ጉም ሙሉ ድሬዳዋን ሲሸፍናት ሳሉት ። እንኳን ሰውን ከሰው ለመለየት ይቅርና ፤ አንተ እራሱ የት እንዳለህ አታውቅም ። ብቻ ወደ ውስጥ እራሱ የምናስገባው oxygen ሳይሆን ክሽን ያለች ንፁህ አዋራ'gen ነው ። (ቅቤ አለው እንዴ ይሄ ነገር ...?) ። ወደ ውጪ ደግሞ በ carbondioxide ፋንታ የምናወጣው አፈር'dioxide ነው ። (እዚጋ chemistry ሲፎርፍ የነበረ ተማሪ ምን እያወራሁ እንደሆነ አይገባውም ...) ። በጠራራ ፀሀይ ድሬዳዋ ከተማ ሙሉ በሙሉ ጨለመች ። የመንገድ ዳር መብራቶች እራሱ ሶላር ናቸውና ሲመሽ በራሳቸው system ነው የሚበሩት ። ዛሬ ግን በቀን የጨለመ መስሏቸው ሲበሩ ውለዋል ። ምሳ ከጓደኞቼ ጋር በልቼ ወደ bank ቤት አመራሁ ። እቅዴ ባንክ ውስጥ ያለኝን ሙሉ capital ማውጣት ነው ። (ይቅርታ small ለማለት ነው...) ። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፤ ሁሌም የማሰለፉበት ባንክ ደረስኩኝና ሰልፉን ተቀላቀልኩ ። የባንክ ቤቱ ጊቢ ባዶ ኪሳቸውን ባሉና ሙሉ ፌስታል ብር በያዙ ሰዎች ተሞልቷል ። ባዶውን የመጣ ኪሱን ሞልቶ ይሄዳል ። ፌስታል ሙሉ ብር ይዞ የመጣ ደግሞ ባዶ ኪሱ ውስጥ ፌስታሉን አስቀምጦ ይመለሳል ። ይሄ ነው እንግዲህ ቁጠባና ቁንጠራ ማለት ። ያለው ሲቆጥብ የሌለው ይቆነጥራል ። ተራዬ ደርሶ ባለፈው የገባልኝን cost #450 ብር አውጥቼ ቀሪውን ብር ሳይ ልቤ በሀሴት ተሞላች ። የማታሳፍር ንፁህ የኢትዮጵያ #27.50 ዶላር አለችኝ ። ቀጣይ ወር ስመጣ ወልዳልኝ #28 ብር እንደ ምትሆንልኝ ተስፋ አለኝ ። ይቺም ብር ሆና ይዣት ወደ አሸዋ አቀናሁ ። (ማነሽ ድሬዳዋን የማታውቂዋ ፡ አሸዋ ደግሞ የሰፈር ስም እንጂ ድንጋይ አይደለም ...) ። ድሬዳዋ ዩኒቨርስቲ ባዶ ሆኖ ካገኛችሁት ብዙም አትደንግጡ ። ምክንያቱም አዳሜና ሄዋኔ የወር አስቤዛዋን ለመሸመት እዚህ አሸዋ ውስጥ ናቸውና ። ተማሪ ፣ አስተማሪ ፣ ነዋሪ ፣ ዘዋሪ እንዳለ ከዚህ ነው የሚሸምቱት ። ኧረ ባለፈው ዘፋኙ Sancho (ታናሞ ካሻሞ ...) እዚህ መጥቶ ለ clip የሚሆኑትን ጫማዎች ገዝቶ ሄዷል አሉ ። ደግሞ ለራሱ ብቻ አይደለም ። ለኔ ጊልዶ እና ያሬዶ ጭምር ይዞ ሄዷል ይባላል ። (አሉባልታ አይደለም ደግሞ ፤ አሉ ብሎ የነገረኝን ልጅ አምነዋለሁ ...) ። brand ጫማ ፣ ልብስ ፣ electronics ፣ ወዘተ እዚህ በርካሽ ዋጋ ይገኛል ። (ኧረ ጀለሴ ፡ ማስታወቂያ ውስጥ ገባሽ እኮ ...። አይኔን ጨፍኜ cost ላይ #250 dollar ጨምሬ vans ጫማ ገዛሁ ። ምሽት ላይ እራት ከጓደኞቼ ጋር በልተን ወደ ዶርም ተመልሰን telegram ገብቼ ከህይወት ጋር ማውራት ጀመርን ከኔ ጋር የምታወራቸው እያንዳንዷ ቃላት ሀይል አላቸው የዋህነቷ ፍቅሯ ፣ ድምጿ ፣ ሁሉ ነገሯ ከአቅሜ በላይ ናቸው ። ደግሞ ነገ አባቷ የሆነ ቦታ እሄዳለው ስላሏት እቤታቸው መምጣት እንደ ምችል ነግራኛለች "ና ናፍቆኛል ትያለሽ አሉ ፡ የኔንም ላንቺ ባወሩ ፣ ካንቺ ብቻ ሰምተው መጡ ፡ ሳይነግሩሽ የኔን በቅጡ ።ሊመሻሽ ሲል #11 ሰዓት አካባቢ ከህይወት "አባዬ ወቷል መምጣት ትችላለህ" የሚል txt ገባልኝ ደቂቃ ሳላባክን ከዶርም ተነስቼ ፣ በቶኒ በር ወጥቼ ሰፈራቸው አካባቢ ደረስኩኝ ። ወደ ቤታቸው በር ቀርቤ ላንኳኳ ስል መሬት ላይ ፖስታ አገኘሁ ማንኳኳቱን ትቼ እሱን አነሳሁትና ከፍቼ ማንበብ ጀመርኩኝ "የፃፍኩልህን አቅጣጫ ተከትለህ ና አታስጠብቀኝ እሺ የኔ ጌታ" ይላል ህይወት እንደሆነች ተረዳሁና ሰፈሩን አንድ ጊዜ ዞር ዞር ብዬ ከቃኘሁ በዋላ በፃፈችልኝ GPS መሠረት መጓዝ ጀመርኩኝ ቤታቸው የተሰራው ወደ መጨረሻ አካባቢ ሲሆን ፡ ከቤታቸው በታችኛው በኩል ትንሽዬ ጫካ መሳይ በዛፎች የተሸፈነ ቦታ አለ አቅጣጫውን ስከተል በስተመጨረሻ ጫካው ውስጥ እራሴን አገኘሁ ፀጥታው ድምፅ አውጥቶ ጆሮዬ ላይ መጮህ ጀመረ ልቤ ከልክ በላይ ይመታል እየመሸም ስለሆነ በጣም ያስፈራል ወዲያው የኮሽታ ድምፅ ከጫካው ውስጥ ይሰማኝ ጀመር የረገፉ የዛፎች ቅጠል በእግር ሲረገጡ የሚፈጠረው ድምፅ ከደቂቃ ወደ ደቂቃ በደንብ ይሰማኝ ጀመር ስለመሸ ብዙ ነገሩ በደንብ አይታይም ኮሽታው በጀርባዬ በኩል እንደሆነ ተረዳሁና ድምፁን ወደ ሰማሁበት አቅጣጫ ስዞር ጭንቅላቴን ምን እንደሆነ የማላውቅ ነገር በሀይል መታኝና ተዘረርኩኝ ለስንት ደቂቃ ወይንም ሰዓት እራሴን እንደሳትኩ አላውቅም ግን እራሴን ጨለማ ክፍል ውስጥ ወንበር ላይ ተቀምጬ ፣ እግሮቼና እጆቼ ወደዋላ ታስረው ነው ያገኘሁት ሳላስበው ፊቴ ላይ የእጅ battery ብልጭ አለብኝና አይኔን አቃጥሎኝ ጭንቅላቴ ውስጥ ብልጭ ብልጭ የሚሉ የተለያዩ የመብራት ቀለሞች ይመላለሱ ጀመር ከላይ እስከ ታች በያዘው ባትሪ scan አደረገኝ ወይ ቤቱ ስለጨለመ ይሁን ወይም ደግሞ ሙሉ በሙሉ ጥቁር ልብስ ለብሷል መሠለኝ በደንብ አይታይም ባትሪውን እንዳበራብኝ በቀኝ እጁ ግንባሬ ላይ ሽጉጥ ደቀነብኝ አይኔ ላይ ስላበራው ማን እንደሆነ እንኳን አይታወቅም ። ወፈር ባለና በሚያስፈራ ድምፅ "በዚህ ዕድሜ ፡ መሞት ትፈልጋለህ ?" አለኝ አልፈልግም' ስለው "መኖር የምትፈልግ ከሆነ የምልህን ነገር ማድረግ ይኖርብሃል" አለኝ ። ፈራ ተባ እያልኩ 'ምን እንዳደርግ ነው የምትፈልገው ?' አልኩት እሱም "ህይወትህን የምትፈልግ ከሆነ የማዝህ ነገር በጣም ቀላል ነው" ሲለኝ 'የምትለኝን ባላደርግስ...?' አልኩት በንዴት ። እሱም "ወይ እዚሁ ግንባርህን ብዬክ ፤ ወይም ደግሞ እስር ቤት ለዘላለም እንድትማቅቅ አደርግሃለሁ" አለኝ የእስር ቤቱ ገርሞኝ 'እንዴት አርገህ ነው ደግሞ እስር ቤት የምታስገባኝ ?' አልኩት የስላቅ ሳቅ እየሳኩኝ ። እሱም እየተሳለቀብኝ "እረሳህ እንዴ ደፍረህ የገደልካትን ልጅ" ሲለኝ ደንግጬ 'የምን ልጅ አልኩት ?' እሱም "አቅጣጫውን ተከትለህ ወደ ጫካው ስትገባ ከዋላህ ሆኜ በካሜራ ሳነሳህና ስቀርፅህ ነበር ። ጫካው ውስጥ ደግሞ የሆነች ልጅን እራሴው ደፍሬ ገድያታለሁ ለማስረጃ ደግሞ የእጅ ሰዓትህንና የአንገት ሀብልህን ቦታው ላይ አስቀምጫለሁ ። ስለዚህ አሁን የምልህን ነገር ካላደረክ በአንድ የስልክ ጥሪ ለፖሊስ አሳልፌ ልሰጥህ እችላለሁ" ሲለኝ በድንጋጤ ፈዝዤ ቀረሁ ። በዚህ መሀል ግን ህይወት የሆነ ቀን ከዲያሪዋ ላይ ያነበበችልኝ ትዝ አለኝ

✎ ክፍል ሀያ አምስት ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።
ይ................
ቀ..................
ጥ...................
ላ....................
ል....................
አሪፍ አሪፍ ግጥም እና ታሪክ ለማግኘት
@Addisu32
@Addisu32
@selafeker
5.8K viewsAddisu, 04:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-01 07:41:34 ​#የከንቲባው_ልጅ

ክፍል 23

ሁሉም ተማሪዎች calculator ይዘው ነው የመጡት ። እኔ ግን በህልሜ የመረቀንኩት አለቀቀኝም መሰለኝ ብዕር እንኳን አልያዝኩም ። ብዕሩን እንደምንም ከመምህር አግኝቻለሁ ። calculator ቀድሞውኑ ለድምር አያስፈልገኝም ፤ አየር ላይ አጫውተዋለሁ ። ብዙ ጊዜ ተማሪ ፈተና ሲደርስ ሲጨናነቁ አያለሁ ። እኔጋር ግን እሱ የለም ። የምችለው ከሆነ እሰየው ፤ ካልሆነ ግን ሲፈልግ ገደል ይግባ ። (ፈተናው ሳይሆን አንተ ነህ ገደል የምትገባው... ) ። ፈተናው ተሰጠንና አየሁት ። #5 ጥያቄ ነው ። ከነሱ ውስጥ ግን እኔ ከአንደኛው ጥያቄ ውጪ አንድም info የለኝም ። እያንዳንዳቸው #4 ፣ #4 ነጥብ አላቸው ። ስለዚህ ከ #20% ውስጥ #4% ነው የማገኘው ማለት ነው ። የማውቃትን #1 ጥያቄ ሰርቼ የቀሩትን ደግሞ ከልጆች copy paste ላደርግ ብዬ ቀና ስል #2 አስተማሪዎች አንዱ ከፊት ሌላኛው ደግሞ ከዋላ ሆነው ድምበር እየጠበቁ ነው ። ጥሎብኝ ፈተና ሲከብደኝ መጨናነቅ አልፈልግም ። የቀሩትን #4 ጥያቄዎች በመሰለኝና ደሳለኝ ሞልቼ ወጣሁ ። ከሳምንታት በፊት "ምነው አንተ ልጅ እያሽቆለቆልክ እኮ ነው ፣ በጣም ከስተሃል" ባሉኝ አንደበታቸው ዛሬ ግን class ውስጥና መንገድ ላይ ያገኙኝ ልጆች እንዳለ "ምን ተገኘ ደግሞ ፡ በጣም ተስማምቶሃል" እያሉኝ ያልፉኝ ጀመር ። እንደውም የተመልካች አይን ሲበዛብኝ ሰግቼ ትፉልኝ ማለት ጀመርኩኝ ። እነሱ ግን ትፉልኝ እና ትፉብኝ መለየት ስለከበዳቸው በዋላ ላይ ማስታጠብያ ገዛሁና እሱ ውስጥ እንዲተፉልኝ አደረኩ ። ሁሉም የውፍረቴን ምክንያት ቢጠይቁኝም ፡ እኔ ግን ትንፍሽ አላልኩም ። ምክንያቱም ከዚህ በፊት ስከሳ አንድም ሰው የክሳቴን ምስጢር አልጠየቀኝምና ። ዶርም መሄድ ስላስጠላኝ ወደ Library አቀናሁ ። የተባረከው ቤተ ክርስቲያን ሄዶ ንሰሐ ይገባል ፤ እንደኔ አይነቱ ደግሞ ቤተ መፅሐፍት ገብቶ ላይገባው ግራ ይጋባል ። Final ፈተና እየደረሰ በመሆኑ ሶስቱም የጊቢው Library እንደ አባይ ሞልተው ተማሪዎች ወደ ግብፅ እየፈሰሱ ይገኛሉ ። አሁን ያለሁት ከሶስቱ አንዱ በሆነውና ዘንድሮ ተመርቆ ስራ በጀመረው Central Science and technology Library ውስጥ ነው ። ይሄ ቤተ መፅሐፍት ግን በጣም ዕድለኛ ነው ። ስንቱ ተምሮና ተመርቆ ስራ ባጣበት ዘመን ላይ ነው ሳይማር ተመርቆ ስራ የጀመረው ። anyways እኔ እንኳን የገባሁት እንደ ሌሎቹ የትምህርት መፃፍ ላነብ አይደለም ። ላይብረሪው ከትምህርት መፅሐፍ ውጪ ፡ ጋዜጣ ፣ መፅሔት ፣ FB ፣ Telegram ፣ ወዘተ መጠቀምያ ቦታ አለው ። ያውም እንደ ሳሎን በሶፋ የተሽቆጠቆጠ ቦታ ። እና ብዙ ጊዜ እዚህ እየመጣሁ Telegram ስለምጠቀም ላይብረሪስቶቹ ጭምር ሸምድደውኝ እንደ ድንገት እንኳን አርፍጄ ቦታው ላይ ሰው ሊቀመጥ ሲመጣ "ሰው አለው" ማለት ጀምረዋል አሉ ። እዚህ የሚገኙ ጋዜጦች ግን አይመቹኝም ። ከነሱ ይልቅ የድሬዳዋ ዩኒቨርስቲ ሽንት ቤቶች ግድግዳ ላይ በተለያዩ የጊቢው Activist ተማሪዎች የሚፃፉት ሺህ እጥፍ ይማርካሉ ። ብዙ ጊዜ እንደውም የETV ዜና ሲናፍቀኝ ወደ ሽንት ቤት ጎራ እልና አነባለሁ ። ወደ ውስጥ ሳትዘልቅ ገና ከበሩ መግቢያ ላይ ይጀምራል ። "እንኳን ወደ ተመስገን በየነ የምግብ ማስወገጃ አዳራሽ በደህና መጣችሁ ። እናንተ ብቻ ጠንክራችሁ ብሉ እንጂ እኛ የናንተን የከበሩ ማዕድናት ለመቀበል #24 ሰዓት ዝግጁ ነን ። ለደንበኞች ቦታ ይያዛል ፣ በተጨማሪም በራሳችን ጉልበት ውሃ ወደ ሽንት ቤቱ እንደፋለታለን" ። ወደ ውስጥ ገብታችሁ ሱሪ አውልቃችሁ ቁጭ ስትሉ ደግሞ በአምስቱም አቅጣጫ (ከፊት በር ላይ ፣ ከዋላ ፣ በቀኝ ፣በግራ እና ኮርኒስ ላይ) ከሽንት ቤቱ ውጡ የማያስብሉ ምርጥ ምርጥ ቀልዶችን ያገኛሉ ። ከሁሉም ግን እኔን የምትመቸኝ "ለዚሁ ነበር እንደዛ የበላሁት ...? " የምትለዋ ነች ።

ምሽት ላይ እራት ከጓደኞቼ ጋር በልተን ቶኒ ላይ ሻይ ጠጥተን #01:30 ወደ ዶርም ስንመለስ ህይወት ደውላልኝ telegram እንድገባ ነገረችኝ ። ቀኑን ሙሉ ያልደወለችልኝ አባቷ እቤት ስለዋሉ እንደሆነና በቅርቡ ደግሞ ከሀገር እንደሚወጡ ነገረችኝ ። አብዛኛው ወሬዋ ግን ናፍቆት ነክ ነበር ። እንደውም በ voice ጭምር እየዘፈነች ልካልኛለች ። Studio ሳትገባ ዝምብላ እንደ ቀልድ የምትልክልኝና እቤቷ እያለሁም የምታዜምልኝ ሙዚቃዎች ህይወት አላቸው ። እሱ ብቻ አይደለም ፤ የምትፅፍልኝ መልዕክቶች ጭምር ልቤን ያቆሙታል ። "ቀኑን ሙሉ ስላንተ ሳስብና ስፅፍልህ ነበር የዋልኩት" ብላኝ ይሄን መልዕክት ላከችልኝ ። "ከዋክብትንና የምድር አሸዋን መቁጠር ከሚሳንህ በላይ ላንተ ያለኝን ስሜት በቁጥር ማወቅ ያዳግትሀል ። በዚች ምድር ላይ ለመኖር #1ሺህ ምክንያቶች ላያስፈልጉኝ ይችላሉ ። ባይሆን ያንተ መኖር ብቻ በራሱ በቂዬ ነው ። አንተ የቀኔ ፀሀይ ነህ ፤ ብሩህ ታደርግልኛለህ ። የምሽቴም ጨረቃ ነህ ፤ ጨለማዬን ትገፍልኛለህ ። ልቤ ፣ ደምስሬ ፣ አይምሮዬ ፣ ንግግሬ ፣ ልብ ምቴ ፣ ህይወቴ ፣ ሁሉ ነገሬ ውስጥ ገብተሃል ። ሌላው ይቅር ፡ አይኔን እንኳን ስጨፍን የምትታየኝ አንተ ነህ ። ብዙ ጊዜ ስትጎጂ እና ስታለቅሺ ማየት አልፈልግም ብለኸኛል ። የኔ ጌታ እየተጎዳሁና እያለቀስኩ ነው የዋልኩት ። አውቃለሁ አጠገቤ መሆን ስላልቻልክ እንጂ እኔን ለመጉዳት እንዳልራከኝ ። ቢሆንም ግን በጣም እየፈራሁ ነው ። ህይወት ላንተ ናት ፡ ሞት ግን ለኔ ፣ ደስታ ላንተ ነው ፡ ሀዘን ግን ለኔ ፣ አብሮ መሆን ላንተ ፡ ብቸኝነት ግን ለኔ ፣ ሁሉ ነገር ላንተ ፡ አንተ ግን ለኔ ነህ ። አንተን መናፈቅ ያስደስታል ፤ ለዛም ነው ቀኑን ሙሉ የማስብህ ። ምሽት ላይ ሆኜ አንተኑ ሳስብህ ከዋክብት አዝነውልኝ ሊያፅናኑኝ ከሰማይ ላይ ይረግፋሉ ። ምናልባት ሰማይ ባዶ ሆና ካገኘሀት ብዙም አትደነቅ ። ምክንያቱም በደምብ እንዳስብህ አድርገህኛልና ። ቀኑን ሙሉ ድምፅህን ሳልሰማ ፣ አይኖችህን ሳላይ ፣ በናፍቆት አሳለፍኩኝ ። ረስተኸኝ ይሁን እያልኩ እጨነቃለሁ ። የኔን ስሜት ሳልነግርህ ከማንም በላይ ታውቀዋለህ ብዬ አስባለሁ ። አብጄ አማኑኤል ብገባ እራሱ አንተን መርሳት የሚቻለኝ አይመስለኝም ። ደግሞ ህይወት መልሳ እንደምታገናኘን እና ወደፊት አንድ ቀን አብረን እንደ ምንህን ተስፋ አደርጋለሁ ። በህይወት መንገድ ላይ መመለስ የለም ፤ ጉዞው ወደፊት ብቻ ነው ። በመንገዴ ውስጥ ብዙ ሰው ላይኖር ይችላል ። ለኔ ግን እሱ አያሳስበኝም ። ነገር ግን የኔ ጌታ ፡ ያንተ አለመኖር ያማል ። ከአለም ጋር ከተለያየን ቆየን ፤ ምክንያቱም የኔ አለም አንተ ነህ ። ፀሀይ ፊቷን አዙራብኝ ብርሃን ካጣሁ ቆይቻለው ፤ ምክንያቱም የኔ ፀሀይ አንተ ነህ ። ጨለማ ውስጥ ነኝ ፣ ምንም አይታየኝም ። ጭር ያለ ቦታ ነኘ ፤ ምንም አይሰማኝም ። እልም ያለ በረሃ ውስጥ ነኝ ፤ በውሃ ጥም ልሞት ነው ። ቀኑንና ለሊቱን መለየት ከብዶኛል ። በቶሎ ላገኝህ ብዬ ተኝቼ አሁንስ ነጋልኝ ስል ተመልሶ ይጨልማል ። እኔ አንተን ሳጣህ እንኳን ቀኑን እራሴንም እረሳለሁ ። ግን የኔ ጌታ እስካሁን ድረስ ያልረሳሁት #

1 ነገር አለ ። እሱም አንተ ነህ ። ምክንያቱም አንተን እረሳሁ ማለት በህይወት የለሁም ማለት ነው" ። ይሄን ሁሉ ብላኝ ፣ በድምጿም እየዘፈነች ልቤን ብታቆመውም የኔ መልስ ግን ዝምታ ነው ። ዝም ....ይቀጥላል
@Addisu32
@selafeker
4.8K viewsAddisu, 04:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-29 08:22:21 ይሄው እየከፈለ ይገኛል ለኔ ከፍሎኛል እናንተም ሞክሩት
@Addisu32
5.1K viewsAddisu, 05:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-29 08:14:59
5.1K viewsAddisu, 05:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-29 08:07:47
5.0K viewsAddisu, 05:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ