2022-06-26 08:44:59
በከተማዋ አንድ በጣም ምስኪን ሰውዬ ነበር።
ብር ተበድሮ ተበድሮ...መክፈል ያቅተውና ሀሳብ ጭንቀት እረፍት
ያሳጣዋል።
ብድሩ 500 ዲናር ደርሶበታል..እናም አንድ ቀን አበዳሪዎቹ
መጥተው በአንዴው ያፋጥጡት ጀመር ...
እሱም ወደ አንድ ነጋዴም ይሄድና በተወሰነ ግዜ እንደሚመልስለት
ቃል ገብቶ ከሱ 500 ዲናር ይበደርና ላስጨነቁት አበዳሪዎቹ
መለሰላቸው።
ቀናት እና ሌሊቶች ይነጉዱ ጀመር ባላሰበው መልኩ የቀጠሮው
ቀን እየተቃረበ መጣ..
ግን ይህ ምስኪን ምንም ያዘጋጀው ነገር የለም።ይልቁንም
ገና ለገና ለቤተስቡ ድጎማ ለሌላ ብድር ተዳርጓል።
ቀኑ ደረሰ ያአበዳሪ መጣና ብሩን ሲጠይቀው ብድሩን መመለስ
አልቻለም።
ነጋዴውም ለከተማዋ ቃዲ/ፍርድ ቤት ዳኛ ጉዳዩን ያቀርብና
ሰውየውን ችሎት አስቆመው...
የፍርድ ቤቱም ዳኛ ጉዳዩን ከተመለከተ በኋላ ተበዳሪው ብድሩን
እስኪመልስ ድረስ እስር ቤት እንዲቆይ ትዕዛዝ አስተላለፈ።
ይህ ምስኪንም ዳኛውን፦
"እባክህ አንድ ቀን ስጠኝ መታሰሬን ለባለቤት እና ለቤተስቤ
ልንገራቸው በፍለጋ እንዳይደክሙ" ይለዋል።
ዳኛውም "ዋስ አምጣ" አለው።
ያን ግን ግዜ ይህ ምስኪን ዋስ ሚሆነው ሰው በአጥገቡ
አላገኘም...
"የኔ ዋስ ነቢያችን ሰ.ዐ.ወ ናቸው። እነሱን ዋስ አድርጌ ነገ
ባልመጣ ከሳቸው ኡመት እንዳልሆንኩ በዱንያም በአኼራም
መስክርብኝ" አለው
ዳኛውም የዋስትናውን ትልቅነት ተረድቶ ዋስትናውን ተቀበለ።
ሰውየውም ወደ ቤቱ ተመለሰ
የሆነውን ሁሉ ለባለቤቱ ነገራት።
ሚስቱም እንዲህ አለችው፦
"በል ከፍርድ ቤት በረሱል ሰ.ዐ.ወ ዋስትና እንደወጣህ ሁላ አሁን
በሳቸው ላይ አብረን ስለዋት እናውርድ አላህ በሳቸው በረካ ከዚህ
ጭንቀት ሊያወጣን ይችላል። አለችው
(ገራሚ ሚስት ናት ወላሂ)
ከዛም በዚህ ተስማሙ አብረው ሰለዋት ማለትም ጀመሩ....
የሰው ልጅ ደካማ ነውና እዛው እንቅልፍ አሸንፎ ወስዳቸው።
ከዚያም በዚህ ሰውየ በህልሙ ረሱል ሰ.ዐ.ወ ይመጡና፦
"ሲነጋ የከተማዋ አስተዳዳሪ ጋ ሂድና ሰላምታዬን
አድርስልኝ።እንዲህም በለው፦ {ረሱል ሰ.ዐ.ወ ብድሬን
እንድትከፍልልኝ አዘውሀል። ምናልባት ምልክትህ ምንድነው ካለህ
አስተዳዳሪው ሁሉ ቀን በኔ ላይ 1000 ሰለዋት ያወርዳል ዛሬ
ቁጥር ላይ ተሳስቶም ነበር አላህ እንደሞላለትም ነገረው} " አሉት።
ሰውየው ገና ከመንጋቱ አስተዳዳሪው ቤት ሲሮጥ ደረሰ።
አስተዳዳሪው ዘንድ እንደደረሰ
"የአላህ መልዕክተኛ ሰላም ብለውኻል። የእኔንም ብድር
እንድትከፍልልኝ አዘውኻልም።"
አለው
አስተዳዳሪው፦ስንት ነው ብድርህ?
ሰውየው፦500 ዲናር
አስተዳዳረው፦እውነት ስለመናገርህ ምንድነው ምልክቱ?
ሰውየው፦ሁለት ምልክቶች አሉኝ አንደኛው አንተ በቀን 1000
ሰለዋት ታወርዳለህ...
አስተዳዳሪው፦ልክ ነህ (አንገቱን ደፍቶ እያለቀስ)
ሰውየው፦ሁለተኛዋ ደሞ ትናንት ስለዋት ስታወርድ በቁጥር
ተሳስተህ ነበር እሷንም አላህ ሞልቶልሀል።
አስተዳዳሪው እያለቀሰ ልክ ብለሀል አለው።
ኪዚያም ከሙስሊሞች ግምጃ ቤት 500 ዲናር እንዲሰጠው አዘዘ
ከግል ንብረቱ ደሞ 2500 ዲናር ሰጥቶ ይህ የኔ ስጦታ ነው ብሎ
አሰናበተው።
ሰውየው ከአስተዳዳሪው ቤት ፊቱ በደስታ ተሞልቶ ይወጣና
ትናንት የገባውን ቃል ሊሞላ ሩጫ ወደ ፍርድ ቤት ይጀምራል...
ፍርድ ቤት ደረሰ...ዳኛው ጋ ሲገባ ዳኛው በከረጢት ብር ይዟል።
ብድርህን እኔ እከፍልልሀለሁ ይህን 500 ዲናር ያዘው ስጦታ
ነው። ባንተ በረካ ረሱልን ዐ.ሰ አይቻለሁ "የዚህን ሰው ሀጃ
ከተወጣህለት የውመል ቂያማ ሀጃህን እንወጣልሀለን" ብለውኛል
አለው።
ያን ግዜ አበዳሪውም ድንገት ብቅ አልና እንዲህ አለ፦" ብድሩን
አውፍ ብየዋለሁ ይህ 500 ዲናር ከኔ ስጦታ ነው ረሱል ዐ.ሰ
በህልሜ "ይህን ሰው አውፍ ካልከው የቂያማ እለት አውፍ
ትባላለህ" ብለውኛል አለ።
ሰውየው ደስታውን መቆጣጠር አቅቶት ወደ ባለቤቱ ሩጫ ቀጠለ
የሆነውን ሁሉ አጫወታት..
በአላህ እርዳታ ትናንት በ500 ዲናር ሊፈረድበት የነበረ ሰውዬ ዛሬ
4000 ዲናር ይዞ ቤቱ ገባ...
__
ሼር በማድረግ ለወዳጅ ዘመዶዎ ያድርሱ
t.me/samihni
75 views05:44