Get Mystery Box with random crypto!

ለሸይኽ ሀሰን ገላው ሀፊዞሁሏህ #ያን_አሊም_ፍቷቸው__!! ----------------------- | አንዳንዴ

ለሸይኽ ሀሰን ገላው ሀፊዞሁሏህ

#ያን_አሊም_ፍቷቸው__!!
-------------------------------
ፅንፈኞች ጎንደር ላይ አማኝን ሲገድሉ፡
በሳጂዶቻችን በቀን ሲቃጠሉ፡
ሞጣላይ መስጂዱ ተቃጥሎ ሲጨፈር፡
ይህ ሁሉ ሲፈፀም ምንም ሳይታፈር!!

ምን አይነት በደል ነው ሽማግሌ ማሰር፡
ሁሌ ከሙስሊም ላይ ደፍሮ ጣት መቀሰር፡
ይህን ተመልክቶ ዝም እያለ መንግስት፡
አሊሞቻችን ላይ መቀየር እንደ እስስት፡

ይህ አይነት ግፋችሁ የጤና አይመስለንም፡
ሊቆቻችን ታስረው ሰላም አንሆንም፡
እንለምናችሁ ፍቱልን አሁንም፡

አልያ ግን እመኑኝ

የሀበሻ ምድር በኛ ደም አትጠራም፡
ሙስሊም ተጨቁኖ ጠላት ስራ አይሰራም፡
አይጨፍርብንም የማንም ሰካራም፡

የኛ አስተማሪወች ፖለቲካ አይሰብኩም፡
ቁጥብ ንፁህ ናቸው የሰው ሀቅ አይነኩም፡
ሙስሊም መሆን ወንጀል ካልሆነ በስተቀር፡
እቅድ አውጥታችሁ ወደ ኋላ እንድንቀር፡

የእምነት ቦታችንን መስጂድ አቃጥላችሁ፡
ይሔ የግፍ ጣራ ሳያሳፍራችሁ፡
ድጋሜ በድፍረት ይህን ከሰራችሁ!!
ያንን ታላቅ አሊም ይፋ ካሰራችሁ!!
በርቱ ቀጥሉበት በዚሁ ያፅናችሁ!!

ከንግድህ ከናንተ ፍትህ አንጠብቅም፡
እስክንሞት ድረስ ግን አንላቀቅም፡
የክልሉ መንግስት ኢስላምን ለማጥፋት፡
ደግሞም ሙስሊሞችን አንገት ለማስደፋት፡
ያው እየሰራ ነው በጥፋት ላይ ጥፋት፡

ለጋ ፖለቲካ አጓጉል ኳሊቲ፡
የምላስ ነጋደ አፀያፊ ፓርቲ፡
ይህ ነው የክልሉ ግሩም prosperity፡

ፍቷቸው ያንን ሊቅ የኛን ታላቅ ሞራል፡
አልያ ግን ጠብቁ መጭው ሸን ያስፈራል፡
ዘላለም እናንተን ስንለምን አንኖርም፡
ሐቅና ባጢሉ መለየቱ አይቀርም፡
ያለ ምንም መስፈርት ፍቷቸው በፍጥነት፡
ሙስሊሙ በሀገሩ ይሰማው ነፃነት፡

የሰላም መምህር ሽማግሌ ናቸው፡
ለምን ይሆን ታዲያ እንድህ መሆናቸው፡
ለምን ይሳቀቁ በውድ ሀገራቸው፡
ችግር ሳይባባስ ያን አሊም ፍቷቸው፡

#በኑረዲን_አል_አረቢ

መንግስት የሚያስረን በሙስሊምነታችን እንጂ በውስጥ ሽርኩቻችን አይደለምና ሁላችንም ድምፅ እንሁን እላለሁ።

http://t.me/nuredinal_arebi