2022-05-05 17:55:21
#አትፍረድ
=====
ይህ ቃል ብዙ ጊዜ ትክክል ባልሆነ መልኩ ጥቅም ላይ ሲውልን ይስተዋላል። ቃሉ ደግሞ ብዙ ጊዜ ጥቅም ላይ ሚውለው አንዳንድ ሰዎች ትክክል ያልሆነ ተግባር ሲፈፅሙ ለዚያ ድርጊታቸው ሲተቹ፣ ሲነቀፉ ያ ድርጊታቸው ልክ እንዳልሆኑ ሲነቀፉ ለድርጊታቸው ማምለጫ ወይም እነሱን ሚደግፉ ሰዎች እንደማገዝ መስሏቸው ያንን ድርጊት መሸፈኛ አትፍረድ፣ አንተን ማን ፈራጅ አረገህ ይላሉ።
ለመሆኑ ፍርድ ምንድነው? የቃሉ ታሪካዊ አመጣጥስ ምንድነው?
ፍርድ የሚለው ቃል ከህግ ጋር ቀጥታ ግንኙነት ያለው ቃል ነው።
ፍርድ ለመፍረድ ህግ ያስፈልጋል ሚፈረደውም ህጉን መሰረት ተደርጎ እንጂ ያለ ህግ አንድ አካል ላይ መፍረድ አይቻልም ። ምክንያቱም ፍርድ የአንድ ህግ የመጨረሻኛው ውሳኔ ነውና።
አንድ ሰው ከመሬት ተነስቶ ፍርድ በራሱ ሊፈርድ አይችልም።
ፍርድ ለአንድ ነገር የመጨረሻ ውሳኔ የሚሰጥ ውሳኔ እንጂ ትችት መሰንዘር አይደለምና።
አሁን በ21ኛው ክፍለ ዘመን ያለውን ለጊዜው እንተውና ወደ መፅሀፍ ቅዱስ ጎራ ብለን ትክክለኛውን ትርጉምና አጠቃቀም ትንሽ እንይ እስቲ ምክንያቱም ብዙ ጊዜ ይህንን ቃል ሚጠቀሙ ሰዎች አትፍረድ የሚለውን መሰረት ሚያደርጉት መፅሀፍ ቅዱስን ስለሆነ ።
እግዚአብሔር አምላክ ለህዝበ እስራኤል ህግ በሙሴ አማካኝነት የሰጠው ህግ ነው( ዘፀአት 20፣ ዘዳግም 6) እግዚአብሔር ለሙሴ ከሰጠው ህግ ሲሆን አስርቱ ትዕዛዛት በመባል ይታወቃል። ከዚህም በተጨማሪ ከዘፍጥረት እስከ ዘዳግም ያሉት አምስቱ መፅሀፍ የህግ መፅሀፍት(Pentateuch ወይም Tora)በመባል ይታወቃሉ። ከዚህ መነሻ ተነስተን እግዚአብሄር ለሙሴ ህግን ሲሰጥ ለህጉ ተገዢ የሆኑትን ሲያመሰግን ህጉን ለሚጥሱት ምን ቅጣት እንደሚያስከትል በእነዚህ አምስቱ የህግ መፅሀፍት በግልፅ ሰፍሯል። በእነዚህ ህግ መፅሀፍት ላይ ህጉን ለሚተላለፉ ሙሴ እንዲፈርድ ፍርዱም ምን እንደሆነ በግልፅ ተፅፏል። ለዚህ ነው በፅሁፌ መጀመሪያ ላይ ፍርድ የህግ የመጨራሻኛው ውሳኔ እንደሆነ የገለፅኩት።ስለሆነም በዚያ ህግ መሰረት አንድ ሰው ህጉን ቢጥስ በህጉ መሰረት ፍርድ ይሰጠዋል።
ለምሳሌ
=====
1.“ሰው በሬ ወይም በግ ቢሰርቅ፥ ቢያርደው ወይም ቢሸጠው፥ በበሬው ፋንታ አምስት በሬዎች፥ በበጉም ፋንታ አራት በጎች ይክፈል።” ዘጸአት 22፥1
ህግ:- አትስረቅ ፍርድ:- አራት ወይም አምስት እጥፍ መመለስ
2. ሄዶም ሌሎች አማልክትን ያመለከ፥ እኔ ላላዘዝኋቸው ለፀሐይና ለጨረቃ ለሰማይም ሠራዊት ሁሉ የሰገደ ቢገኝ፥
⁴ ቢያወሩልህም ብትሰማም፥ ያንን ፈጽመህ መርምር፤ እነሆም፥ እውነት ቢሆን፥ በእስራኤልም መካከል እንዲህ ያለ ርኵሰት እንደ ተሠራ እርግጥ ሆኖ ቢገኝ፥
⁵ ይህን ክፉ ነገር የሠሩትን ያን ወንድ ወይም ያችን ሴት ወደ በርህ ታመጣቸዋለህ፥ እስኪሞቱም ድረስ በድንጋይ ትወግራቸዋለህ።
ቢያመነዝር በድንጋይ ተወግሮ ይሞታል"
ዘዳግም 17
ህግ:-ሌሎች አማልክት አታምልክ ፍርድ:- በድንጋይ ወግሮ መግደል
ስለዚህም ነው በኢየሱስ ዘመን በዮሐ 8:10 ላይ ስታመነዝር የተያዘችውን ሴት ሊወግሩ ፍርድ ሊሰጡ ተሰብስበው ሊወግሩ(ሊፈርዱ) ፈልገው። ህጉ ወግረን እንድንገድል (የሞት ፍርድ እንድንፈርድ)ያዝዛል አንተ ምን ትላለህ ያሉት።
እነዚህንና ሌሎች የመፅሀፍ ቅዲስ ክፍሎች ስንመለከት ፍርድ ተብሎ የተፃፈው ወይም ሰዎች ሲፈርዱ የነበረው በህጉ መሰረት የመጨረሻ ቅጣት በመስጠት ማለትም በመስቀል፣ በመውገር ወዘተ እንጂ በአፍ በመናገር አይደለም አይደለም።በሌላ አባባል ፍርድ ድርጊት የሚከናወን ስርዓት ነው።
ታዲያ በዚህ ዘመን አንዳንድ ሰዎች ኢ-መፅሀፍ ቅዱሳዊ ልምምድ ሲያደርጉ ቃሉ ያልፈቀደውን ሲያደርጉ ወይም ትክክል አይደለህም ተብለው ሲተቹ ቶሎ ብለው አትፍረድ ይላሉ። ታዲያ ይህ በታሪክም በቅዱስ ቃሉም ስንመዝን ምንም መሰረት የለለው እና ትክክልም ያልሆነ አባባል ነው።
አንድ ሰው ትክክል ያልሆነ ነገር ሲያደርግ ትክክል አይደለህም ማለት ፍርድ ተብሎ አይጠራም ፍርድም አይደለም። መፍረድማ ቢሆን ያ ሰው አመንዝሮ ከሆነ በድንጋይ ወግሮ መግደል ነው። ሰርቆ ከሆነ አራት ወይም አምስት እጥፍ ማስከፈል ነው። ታዲያ አንድ ሰው ሀጢያት ሲሰራ ሰርተሃል፣ ተሳስተሃል ማለት መፍረድ አይደለም?
አወ መፍረድ አይደለም መገሰፅ ይባላል።
ብዙ ሰዎች ተግሳፅን እና መፍረድን ቀላቅለውታል።
የእግዚአብሔር ቃል ሲናገር ለጢሞቴዎስ ዝለፍና ገስፅ ይለናል።
“ቃሉን ስበክ፥ በጊዜውም አለጊዜውም ጽና፥ ፈጽመህ እየታገሥህና እያስተማርህ፥ #ዝለፍና #ገሥጽ ምከርም።”
— 2ኛ ጢሞቴዎስ 4፥2
በሌላም ክፍል ጢሞቴዎስን እንዲህ ይላል።
“ይህን በሙሉ ሥልጣን #ተናገርና ምከር #ገሥጽም፤ ማንም አይናቅህ።”
— ቲቶ 2፥15
ታዲያ አንድ ሰው በስህተት ስራ ወይም ትክክል ባልሆነ ነገር ሲገኝ መንቀፍ፣ ትክክል አለመሆኑን መናገር መገስፅ ቃሉ የሚደግፍ ትክክለኛ መፅሀፉ የሚያዝ ተግባር እንጂ ፍርድ ነው የሚል ድምዳሜ ከየት የመጣ ትርጉም ነው?
ኢየሱስ በአዲስ ኪዳን አትፍረድ ይፈረድብሃል ያለው ዘመነ ኦሪት ሰዎች በህጉ መሰረት የሚፈርዱትን ፍርድ ማብቃቱን እና ፍርድ መጨረሻ እሱ ዳግም መምጣቱን ለማሳየት እንጂ ፍርድ የሚለው አውድ ዛሬ ብዙዎች በሚጠቅሱት አውድ አይደለም።
ዛሬ ብዙዎች ፍርድ ብለው የሚጠሩትን ኢየሱስ በብዙ መልኩ ገስጿል። ለምሳሌ ማቴ 23:13
“እናንተ ግብዞች ጻፎችና ፈሪሳውያን፥ መንግሥተ ሰማያትን በሰው ፊት ስለምትዘጉ፥ ወዮላችሁ እናንተ አትገቡም የሚገቡትንም እንዳይገቡ ትከለክላላችሁ።”
በዚህ ክፍል መንግስተ ሰማይ አትገቡም ይላል ይህ ፍርድ ነው ማለት ነው?
እናንተ ግብዞች ይላል ፍርድ ነው ማለት ነው?
ይህ ፍርድ አይደለም እነዚህ ሰዎች ከስህተታቸው ተመልሰው ትክክለኛውን መንገድ እንዲመለሱ እየገሰጻቸው እንጂ እየፈረደ አይደለም። ፍርድማ ቢሆን ወዲያው መንግስተ ሰማይ እንዳይገቡ ከልክሎ ወደ ገሃነመ እሳት መላክ ነበረበት።
ከላይ በአጽኖት እንደጻፍኩት ፍርድ የመጨረሻ ውሳኔ ነው አንድ ሰው ከተፈረደ ቀጣዩ እርምጃ መተግበር ብቻ እንጂ ሌላ እድል የለውም።
በዘመነ ህግ የነበረው አሰራርም ይህ ነበር። ስለዚህ አንድን ነገር ያለ አውዱ ያለ ቦታው መጠቀም አላጎሪ ነው።
ኢየሱስ ብቻ ሳይሆን ሌሎችም የአዲስ ኪዳን አገልጋዮች ሲያገለግሉ በተመሳሳይ መልኩ ሰዎችን ሲገስጹ ነበር ለምሳሌ
3.እናንተ #የእፉኝት ልጆች (ዮሃንስ ማቴ 3:7))
4. #ውሾች ፊሊ 3:2 (ሀዋሪያው ጳውሎስ)
እነዚህ ሁሉ ለእግዚ/ር የተመረጡ አገልጋዮች በአንዳንሶች ስሌት ፈርደዋል ወይም እየፈረዱ ነው ማለት ነው። እነዚህ አገልጋዮች ፍርድ ምን እንደሆነ ኦሪቱንም ሀዲሱንም ጠንቅቀው ያውቃሉ። ማወቅ ብቻ አይደለም ይህ ድርጊት ተግሳጽ ስለሆነ ቃሉም ገስጹ ብሎ ስላዘዛቸው በመገሰጻቸው አክሊል እንደሚያገኙ ጠንቅቀው አውቀው ነው ሚገስጹት እንጂ ፍርድ እንዳልሆነ የፍርድ ቀን ደግሞ ከክርስቶስ ዳግም ምጽዓት በኋላ እንደሆነ ጠንቅቀው ሚያውቁ ሚያስተምሩም ጭምር ናቸው።
የተሰሎንቄን መጽሀፍ የጻፈው ስለ መነጠቅ ያብራራው በእጅ ስላልተሰራችው በሰማይ ስላለችው መኖሪያ የጻፈው ይህንን ሁሉ የተግሳጽ ቃል ሲያዘንብ ፍርድ መሆኑን ተምታቶበት አይደለም።
476 views14:55