የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ አመራሮች በራያ ቆቦ ወረዳ አራዶም ቀበሌ ሐምሌ 25 ቀን 2014 ዓ/ም የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አካሂደዋል። በችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩ የግብርና ቢሮ ሀላፊ ዶ/ር ሐይለማርያም ከፍያለው፤ የቢሮው ምክትል ቢሮ ሀላፊ ዶ/ር አልማዝ ጊዜው ጨምሮ የቢሮ አመራሮች፤ የሰሜን ወሎ ዞን ግብርና መምሪያ እንዲሁም የራያ ቆቦ ወረዳ አመራሮች፤ ባለሙያዎችና አርሶአደሮች ተገኝተዋል። በተጨማሪ በአካባቢው የሚገኙ የመከላከያ ሠራዊት እና የአማራ ክልል ልዩ ሀይል አባላት በችገኝ ተከላ መርሃ ግብር ተሳትፈዋል። ዝርዝር ዜናውን ይዘን እንቀርባለን 371 views12:47