የሰርጥ አድራሻ:
ምድቦች:
ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች:
931
የሰርጥ መግለጫ
✔አጫጭር መልዕክቶች፣ ጥበብና ግሳፄዎች፣ አስገራሚ ታሪኮች፣ ወርቃማ የሊቃውንት የግል ታሪኮች፣ ግጥሞች፣ የእምነት ትውፊቶችና ሌሎችም በርካታ ነገሮች የሚዳሰሱበት የቴሌግራም ቻናል!!
@qteloch
……………
@fukheyredin
Ratings & Reviews
Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.
5 stars
1
4 stars
2
3 stars
0
2 stars
0
1 stars
0
የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች
2022-02-21 21:20:36
Join
1.2K viewsUbuntu.., 18:20
2022-02-21 21:20:19
https://t.me/qelemmrko
Join
1.1K viewsUbuntu.., 18:20
2022-02-15 22:32:14
በፍቅር ውዱዕ
ናፍቆት ሲያቆመው ከስግደቱ በር
"ምን ቸግሮት ነው" የሚልም ነበር
አወይ ሰው መሆን…
አወይ መወጠር
እንዲህ መጠርጠር።
ያንዳንዱ ባሪያ ከፈጣሪው ጋር የያዘው ፍቅር
በችግር እንጂ ለማይመጣ ሰው ያሰኛል "ይቅር"።
"ምን ቸግሮት ነው?"
(ፉአድ ኸይረዲን)
@qelemmrko
1.2K viewsUbuntu.., 19:32
2022-02-15 14:43:10
ተፈጥሮ ሆኖ
ብገረምብሽ ባደንቅ መልክሽን
አስተውላለሁ
"ምግባር" የሚሉት የሰው ልክሽን።
ይቻለኛል ወይ?
አንቺን ደፍቼ መልክሽን መዝገን
አይሻልም ወይ?
ከማይፈርስ ውበት ሄዶ መወገን።
የሚያኖረን ምግባር
እርሱን ማመስገን
በርሱ መመስገን።
አይሻልም ወይ?
(ፉአድ ኸይረዲን)
1.0K viewsUbuntu.., 11:43
2022-01-10 20:24:12
የምትሰራውን ስራ ፅድቅ እንደሆነ ለማብራራት አትሞክር። እነርሱ የማያምፁ የሰባተኛው ሰማይ መልዓክት አይደሉም፣ ከእግሮቻቸው ስርም ገነት የለም። መስራት ያለብህን ብቻ ስራ… በልብህ ሚዛን፣ በእምነትህ መለኪያ!
@qelemmrko
@qelemmrko
1.3K viewsFu Kheyredin, 17:24
2021-12-31 07:27:37
https://t.me/qelemmrko
Join
1.5K viewsFu Kheyredin, 04:27
2021-12-26 18:16:32
ከወደዱ…
(ፉአድ ኸይረዲን)
ጨረቃን ናፋቂ አይሸሽም ጨለማን
ብርሃን ፈላጊ፣
ትቀልጣለች ብሎ አይተዋትም ሻማን።
ወዳጅ የተባለ…ውበት ተመልክቶ፣
እሾሁን አይፈራም ፅጌሬዳን ሽቶ።
የተሸነፍክ እንደው
ለሀሳብ እምነቷ ለፀባይዋም ጭምር
ስለቁንጅናዋም ባድናቆትህ ዘምር
ምሉዕ ነገር …
በሰውኛ አዳራሽ
አይገኝም ጭራሽ!
@qelemmrko
1.4K viewsFu Kheyredin, 15:16
2021-12-12 21:25:27
በህይወታችን ውስጥ ብዙ ሰዎችን እናገኛለን። አብዛኞቹ ግን ይሄዳሉ። ጥቂቶቹ ናቸው በልብህ የስክነቱ ዓለም ውስጥ "ፍቅርም ክብርም" ኖሯቸው የሚቀመጡት። ጥቂቶቹ ልባችን ውስጥ የተለየ ክፍል ይኖራቸዋል። የጊዜ አቧራም አያተናቸውም። የዘመን ለውጥም አይፍቃቸውም።
@qteloch
@qteloch
1.8K viewsFu Kheyredin, 18:25
2021-12-06 21:35:12
"የኸዲጃን አይነት እንስት ማግኘት ከሻህ ፣ እንደ ሙሀመድ አይነት ሰው መሆን ይኖርብሃል።"
ሙስጠፋ መህሙድ
በህይወትህ ውስጥ ያልሆንከውን አይነት ሰው ፍለጋ አትኳትን፣ ክፍተትህን የሚሞላልህ ክፋይ እንጂ ምሉዕ ማንነት ሽተህ አትድከም። ምሉዕ ብታገኝ እንኳ አንተ ምሉዕ አይደለህምና። መሻትህ በዓላማ ውስጥ መኖር ከሆነ ህይወትንና አንተን የተረዳ ሰው ይበቃሃል።
Fuad kheyredin
@qteloch
@qteloch
1.7K viewsFu Kheyredin, 18:35
2021-12-05 18:03:41
ልጅ እያለን ወላጆቻችን የማንረዳውን ብዙ ምክር ይነግሩን ነበር። ከዚያም እነዚያን ምክሮች የምናልፍባቸው ቀናት በግልፅ ይተነትኑት ጀመር። "ቀድመን በተረዳነው ኖሮ" ያስብሉናል።
@Qteloch
@qteloch
2.0K viewsFu Kheyredin, 15:03