Get Mystery Box with random crypto!

ጥር 01 /2015 ዓ.ም ህይወት በየ Instagram ፎቶ እንደምናያው ሁሌም ድሎት እና ምቾት | QesemAcademy

ጥር 01 /2015 ዓ.ም

ህይወት በየ Instagram ፎቶ እንደምናያው ሁሌም ድሎት እና ምቾት የሞላባት አደለችም! አንዳንዴ  ''እኔ አሁን እየኖርኩ ነው ታሰኛለች? ''

ሰዎች መንገድ ላይ አጊንተው '' ሃይ ፣ ሰላም ነው ?'' ሲሉን ደህና ነኝ እንላለን እውነታው ግን ውስጣችን ህመም መያዛችን ነው! ጠዋት መነሳት -በድብርት ሙድ ውስጥ መዋል-  ማታ መተኛት ፣ ጠዋት መነሳት - በተስፋ መቁረጥ ስሜት ውሰጥ መዋተት- ማታ .... አሰልቺ የሆነ ደባሪ ኑሮ ፣ያማል! አዎ ይህ ሁላችንም ጋር ያለ እውነታ ነው  ፣ ማድረግ የማንፈልጋቸው ነገሮች ካረግን በኋላ እንፀፀታለን ፣ '' ድጋሜ አላረገውም ብሎ ማልቀስ '' ችግሩ ግን መልሰን ያንን ስህተት መስራታችን ነው!  ታጥቦ - ጭቃ መሆን ፣ በጣም ያማል!


አንዳንዴ በራሴ ማድረግ የከበዱኝን ነገሮች ፣ ለእግዚአብሔር መተው ፣ እንደ ሽንፈት ይሆንብኛል! ህይወት ሲሰለቸኝ ፣ ኑሮ ሲያደክመኝ ፣ መከራው ሲበዛ ፣ ጌታዬ ሆይ ፣ አግዘኝ ብሎ ማለት እንኳ ስንፍና መስሎ ይሰማኛል! ወደ ቤቱ መሄድ ተውኩ ፣ አንድ ወር ሆኖኛል ።


ችግሮቼን በራሴ ብቻ ነው መፍታት የምፈልገው! መፅሀፍ አንብቦ ወይ ሰው ጠይቆ ፣ ለችግሩ መፍትሄ ማግኘት! አይገርምም ይሄን ሁሉ ሳረግ እንኳን አምላኬ የረዳኝ አይመስለኝም ፣ወዴት እና እንዴት እንደምሄድ ፣ ምን ማረግ እንዳለብኝ እንኳን አላውቅም ፣ ሁሉንም በራሴ ለማስተካከል ስሞክር መሸከም ከምችለው በላይ ጫናው ከበደኝ! ደከመኝ!

ሰው ለካ ምን አይነት ትዕቢተኛ ነው ፣ ወደ ሳንባው የሚሸጉጠውን ትንፋሽ አስቦ ፤ ከፍሎበት ይመሰል ፣ ይሄን ያክል መመፃደቅ አሁን ምን ይሉታል?ለነገሩ ለካ ሁሉም ሰው አደለም!

ዘግይቶም ቢሆን ትንሽ ትንሽ እየገባኝ ነው  ፣ ያለ እግዚአብሔር ፍቃድ አሁን ላይ መድረስ እንዴት ይቻለኝ ነበር! ''ያለእሱ ከንቱ ነኝ ፣ ....'' እልና ካዲያ '' ለምን እሱ እያለ ይሄ ሁሉ ፈተና በዛብኝ ?'' ብዬ ጠይቃለሁ!  መልሱ ሩቅ አደለም ፣ ሊያስተምረኝ ነው ፣ 'ካዲያ እስከመች ነው ይህ ሁሉ ሲቃይ የሚቀጥለው?''፣ እስክማር! እስኪገባኝ! በስቃይ ውስጥ ያለውን መራራ እውነት እስቀምሰው።



https://t.me/Chalu_A