2022-05-24 08:11:46
#የኢየሱስ_ቅድምና ( #2 )
በአገልጋይ ብርሃኑ ታምራት
ጌታ ኢየሱስ በሥጋ የተገለጠው ከጊዜ በኋላ ከድንግል ማርያም ነው።ይሄ ግን ለመገለጥ ሥጋን መዋሃድን እንጂ ጅማሬን አያሳይም።ኢየሱስ አልፋ ነው። #የመጣውም_ከአለበት_ወደ_አለበት_እንጂ_ከአለበት_ወዳልነበረበት_አይደለም።እንዲህ ተብሎ እንደተፃፈ፦
ዮሐንስ 1
¯¯¯¯¯¯⁹ ለሰው ሁሉ የሚያበራው እውነተኛው ብርሃን #ወደ_ዓለም_ይመጣ_ነበር።
¹⁰ #በዓለም_ነበረ፥ #ዓለሙም_በእርሱ_ሆነ፥ #ዓለሙም_አላወቀውም።
#ወደ_ዓለም_በሥጋ_የመጣው_ኢየሱስ_በዓለም_ውስጥ_የነበረው_ነው። #የነበረው_መጣ።ያልታየው በሥጋ ተገለጠ።ዓለምን የፈጠረውም እርሱ ነው።በዓለምም ነበረ።ዓለም እንዲያየውና የማዳን ሥራውን ለመፈፀምም በሥጋ ተገለጠ።
በሥጋ ተገልጦ መመላለሱን፤ከሴት ተወልዶ የሰው ልጅ መባሉን ያዩ ሕልውናውን በሥጋ ከተገለጠበት ጊዜ ጀምረው እንዳይቆጥሩት "በመጀመሪያው ቃል ነበር…ቃልም ሥጋ ሆነ" በማለት የኢየሱስ ክርስቶስን ቅድምና አሰምቶ ዮሐንስ ተናገረ።
ያመንበት ኢየሱስ አልፋ ነው።ለፍጥረት መጀመሪያን የሰጠ መጀመሪያ የለሽ ቀዳማዊ እርሱ ነው።መጨረሻ የሌለው ዖሜጋም እርሱ ነው።ለፍጥረት ፍፃሜን ይሰጣል።እርሱ ግን ፍፃሜ የለውም።
በለበሰው ሥጋ ዘመን ቢቆጠርለትም በመለኮታዊ ማንነቱ መጀመሪያም መጨረሻም የለውም።
እንዲህ ተብሎ እንደተፃፈ፦
ዮሐንስ 8
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁵⁷ አይሁድም፦ ገና አምሳ ዓመት ያልሆነህ አብርሃምን አይተሃልን? አሉት።
⁵⁸ #ኢየሱስም፦ #እውነት_እውነት_እላችኋለሁ፥ #አብርሃም_ሳይወለድ_እኔ_አለሁ አላቸው።
ደግሞም ባለ ራእዩ ዮሐንስን እንዲህ አለው፦
ራእይ 1
¯¯¯¯¯¯¹⁷ ባየሁትም ጊዜ እንደ ሞተ ሰው ሆኜ ከእግሩ በታች ወደቅሁ። ቀኝ እጁንም ጫነብኝ እንዲህም አለኝ፦ አትፍራ፤ #ፊተኛውና_መጨረሻው_ሕያውም_እኔ_ነኝ፥
¹⁸ ሞቼም ነበርሁ እነሆም፥ ከዘላለም እስከ ዘላለም ድረስ ሕያው ነኝ፥ የሞትና የሲኦልም መክፈቻ አለኝ።
የኢየሱስ ሕልውና(መኖር) ዓለም ከተፈጠረ ዘመን ከተቆጠረ በኋላ ሳይሆን ዓለም ሳይፈጠር ዘመን ሳይቆጠር ነው።
ዓለም ሳይፈጠር ለኖረ፤ዓለምንና በዓለምን ያለውን ለራሱ ለፈጠረ ለጌታ ኢየሱስ ክብር ይሁን።አሜን።።
16/09/2014 የጌታ ዓመት
1.6K views05:11